2010 (እ.አ.አ)
በእግዚአብሔር አብ እና በኢየሱስ ክርስቶስ እምነትን በግል ቅዱስ መጻህፍት ጥናት ማጠናከር
ማርች 2010


የሴቶች የቤት ለቤት ማስተማሪያ መልእክት ፣ መጋቢት 2010 (እ.አ.አ)

በእግዚአብሔር አብ እና በኢየሱስ ክርስቶስ እምነትን በግል ቅዱስ መጻህፍት ጥናት ማጠናከር

እነዚህን ቅዱስ መጻህፍትን እና ጥቅሶችን ወይም፣ አስፈላጊም ከሆነ፣ የምትጎበኗቸውን እህቶች ፍላጎት የሚያሟሉትን ሌሎች መሰረቶች አስተምሩ። ስለትምህርቱም ምስክራችሁን ስጡ። የምትጎብኟቸውንም የተማሩትን እና የሚሰማቸውን እንዲካፈሉ ጋብዟቸው።

“አዲስ ሙሽራ በነበርኩበት ጊዜ፣ …በዎርዴ መፅሐፈ ሞርሞንን ወይም አጭሩን የቤተክርስትያን ታሪክ መፅሀል ላነበቡት የሴቶች መረዳጃ ማህበር እህቶች ወደተሰጠው ምሳ ተጋብዤ ነበር። ቅዱስ መጻህፍትን ማንበቤ ችላ እያልኩኝ ነበር፣ ስለዚህ ወደ ምሳው ለመሄድ ብቁ የሆንኩት ቀላል እና ብዙ ጊዜ የማይፈጀውን አጭሩን መፅሐፍ በማንበብ ነበር። ምሳዬን እየበላሁ እያለሁ፣ ምንም እንኳን የታሪክ መፅሀፉ ጥሩ ቢሆንም፣ መፅሐፈ ሞርሞንን ማንበብ እንደነበረብኝ ስሜታ መጣብኝ። መንፈስ ቅዱስ የቅዱስ መጻህፍት ማንበብ ጸባዬን እንድቀይር እያነሳሳኝ ነበር። በእዚያም ቀን መፅሐፈ ሞርሞንን በየቀኑ ማንበብ ጀመርኩኝ፣ እና በምንም አላቆምኩም። …በየቀኑ ቅዱስ መጻህፍትን ስላነበብኩኝ፣ ስለሰማይ አባቴ፣ ስለልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ እና እነደእነርሱ አይነት ለመሆን ምን ማድረግ እንዳለብኝ ተማርኩኝ። …

“… እያንዳንዷ ሴት በቤቷ ውስጥ የወንጌል ትምህርት አስተማሪ መሆን ትችላለህ፣ እና በቤተክርስትያኗ ውስጥ ያለችው እያንዳንዷ እህት እንደ መሪ እና አስተማሪ የወንጌል እውቀት ያስፈልጋታል። በየቀኑ ቅዱስ መጻህፍት የማጥናት ጸባይ የማይኖራችሁ ከሆናችሁ፣ አሁን ጀምሩ እና በዚህ እና በዘለአለማዊ ህይወቶች ለሚኖራችሁ ሀላፊነት ለመዘጋጀት ዘንድ በማጥናት ቀጥሉ።”1

ጁሊ ቤክ፣ የሴኦትች መረዳጃ ማህበር አጠቃላይ ፕሬዘደንት።

“የቅዱስ መጻህፍት ጥናት ምስክራችንን እና የቤተሰቦቻችንን ምስክሮች ለማሳደግ ይረዱናል። በእነዚህ ቀናት ልጆቻችን ትክክል የሆነውን እንዲያስወግዱ እና በምትኩም የአለም ደስታዎችን እንዲፈልጉ በሚገፋፏቸው ድምጾች ተከብበው እያደጉ ናቸው። በኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል፣ በእውነት ምስክር፣ እና በጻድቅነት ለመኖር ውሳኔነት፣ ላይ ጽኑ የሆነ መመሪያ መሰረት ከሌላቸው በስተቀር፣ ለእነዚህ ተጽዕኖች በቀላል ለመማረክ የሚችሉ ይሆናሉ። እነርሱን መደገፍ እና መጠበቅ የእኛ ሀላፊነት ነው።”2

ፕሬዘደንት ቶማስ ኤስ ሞንሰን።

“እህቶቻችን የቅዱስ መጻህፍት ምሁር እንዲሆኑ እንፈልጋቸዋለን። … ለእራሳችሁ ደህንናት እና የእራሳችሁን ልጆች እና ወደተፀኖአችሁ የሚመጡትን ሌሎች ለማስተማር አላማ ከእነዚህ ዘለአለማዊ እውነቶች ጋር የምትተዋወቁ እንድትሆኑ እንፈልጋችኋለን።”3

“ያገባችሁም ወይም ያላገባችሁ፣ ወጣት ወይም አሮጊት፣ ባል የሞተባቸው ወም ከቤተሰብ ጋር የምትኖሩ ቢሆንም፣ ቤቶቻችን ውዱስ መጻህፍት ምሁር በሆኑ እህቶች እንዲባረኩ እንፈልጋለን። የቅዱስ መጻህፍት ተማሪዎች ሁኑ—ሌሎችን ለመገሰፅ ሳይሆን፣ ሌሎችን ለማነሳሳት።”4

ፕሬዘደንት ስፔንሰር ደብሊው ኪምባል (1895–1985)

ማስታወሻዎች

  1. ጁሊ ቢ ቤክ, “My Soul Delighteth in the Scriptures,” Liahona፣ ግንቦት 2004, 107–9።

  2. ቶማስ ኤስ ሞንሰን፣ “Three Goals to Guide You፣” Liahona፣ ህዳር 2007፣ 118።

  3. ስፔንሰር ደብሊው ኪምባል፣ “Privileges and Responsibilities of Sisters፣” Ensign፣ ህዳር 1978፣ 102።

  4. ስፔንሰር ደብሊው ኪምባል፣ “The Role of Righteous Women፣” Ensign፣ ህዳር 1979፣ 102።

ለሴቶች የቤት ለቤት አስተማሪ እርዳታዎች

በጉብኝታችሁ ጊዜ፣ ጥያቄዎችን ጠይቁ እና አስተያየታችሁን ቅዱስ መጻህፍትን በመጠቀም ተካፈሉ። የቅዱስ መጻህፍት ጥናት እንዴት እምነታችሁ እንዳጠናከረላችሁ ምስክር ስጡ። የምትጎበኟትን እህት እንዴት የቅዱስ መጻህፍት ጥናቷ ቤቷን እና ቤተሰቧን እንዳጠናከረላት ጠይቋት።

የግል ዝግጅት

ዮሀንስ 5፧39

2 ጢማቴዎስ 3፧14–17

2 ኔፊ 9፧50–5131፧2032፧3–5

D&C 138፧1–11

አትም