2014 (እ.አ.አ)
የኢየሱስ ክርስቶሰ መለኮታዊ ተልእኮ፤ የአለም ብርሀን
ማርች 2014


የሴቶች የቤት ለቤት ማስተማሪያ መልእክት፣ የመጋቢት 2014 (እ.አ.አ)

የኢየሱስ ክርስቶሰ መለኮታዊ ተልእኮ፥ የአለም ብርሀን

በጸሎት መንፈስ ይህንን መረጃ አንብቡት እና ምን እንደምታካፍሉ ለማወቅ ጣሩ። የአዳኝንን ህይወት እና ተልእኮ መረዳት በእርሱ ያላችሁን እምነት የሚያሳድገው እና በሴቶች የቤት ለቤት ትምህርት ምክንያት የምትንከባከቧቸውን የሚባርከው እንዴት ነው? ለተጨማሪ መረጃ ወደwww.reliefsociety.lds.org ሂዱ

እምነት • ቤተሰብ • እርዳታ

ኢየሱስ ክርስቶስ የአለም ብርሀን መሆኑን እየተረዳን ስንመጣ፣ በእርሱ ያለንን እምነት እንጨምራለን እናም ለሌሎች ብርሀን እንሆናለን። ክርስቶስ የእርሱን የስራ ፋንታ ለእያንዳንዱ ሰው ሁሉ [የማያበራ] የእውነት ብርሀን መሆን ነው (3. ት. እና ቃ. 93:2) በማለት መስክሯል እና “ወደ አለም ያበራ ዘንድ ብርሀን (የእርሱን) ከፍ አድርጋችሁ ያዙ” ብሎ ጠይቆናል (3ኛ ኔፊ 18፥24)።

ስለ ክርስቶስ ብርሀን ነብያቶቻችንም መስክረዋል። ፕሬዘዳንት ሄነሪ ቢ. አይሪንግ፣ በቀዳማዊ አመራር የመጀመሪያ አማካሪ፣ እንዲህ ብለዋል፥ “የበለጠ እንደ አዳኝ መስሎ ለመኖር መሞከርን በመረጣችሁ ቁጥር፣ ምስክርነታችሁን ታጠነክራላችሁ። ከጊዜም በኋላ እርሱ የአለም ብርሀን እንደሆነ ለራሳችሁ ታውቃላችሁ። … በህይወታችሁ ውስጥ የክርስቶስን ብርሀን ለሌሎች ታንጸባርቃላችሁ።”1

ሽማግሌ ኩዌንቲን ኤል. ኩክ የአስራ ሁለቱ ሐዋርያት አባል እኛ የአለም ብርሀን ስለመሆናችን እንዲህ አሉ፥ “ቤተሰቦቻችንን መጠበቅ አለብን አናም በማህብረሰቦቻችን ውስጥ ብርሀንን፣ ተስፋን እና ግብረ ገብነትን ጠብቆ ለመያዝ የቻልነውን ሁሉ በማድረግ ከሁሉም መልካም ስሜት ካላቸው ሰዎች ጋር ፊት ለፊት መሆን አለብን።”2

ከቅዱሳት መጻህፍት

4. ዮሀንስ 8፥12ትምህርት እና ቃል ኪዳን 50፥24115፥5

ከታሪካችን

የኋለኛው ቀን ቅዱሳን ሴቶች ዛሬም ብርሀናቸውን ከፍ አድርገው መያዝን ቀጥለዋል።

በቻይና፣ሆንግ ኮንግ በሚገኝ ትልቅ ሕንጻ 80ኛው ፎቅ ላይ፣ አንድ ያላገባች አካል ጉዳተኛ የሆነች እህት፣ በቤተሰቧ ብቸኛ የኋለኛው ቀን ቅዱስ የሆነች ሴት፣ እርሷ እና ጎብኚዎች የመንፈስ ቅዱስን ተጽእኖ ሊሰማቸው የሚችሉበትን መጠለያ ቤት ፈጠረች። ቅዱሳት መጽሐፍቶቿን፣ የሴቶች መረዳጃ መመሪያ መጽሐፍቶቿን እና መዝሙር መጽሐፏን በቅርብ አስቀመጠች። ለአለፉት ዘመዶቿ ስርዐቶችን ለመፈጸም ወደ ቤተ-መቅደስ ተጓዘች።3

በብራዚል ውስጥ አንዲት ጻድቅ እናት ልጆቿን በወንጌል ብርሀን ውስጥ አሳደገች። የመጀመሪያ ክፍል መዝሙሮች የቀይ ብሎኬት ቤቷን አየር ሞሉት፣ እና ከLiahona ላይ የነበሩ የቤተ-መቅደሶች፣ የእግዚአብሔር ነብያቶች እና የአዳኝ ምስሎች ግድግዳዎቹን ሸፈኑት። ልጆቻቸው በቃል-ኪዳን ውስጥ ይወለዱ ዘንድ እርሷና ባለቤቷ በቤተ-መቅደስ ውስጥ ለመታተም መስዋትነትን ከፈሉ። በወንጌል ብርሀን፣ እውነት እና ጥንካሬ ውስጥ ልጆቿን እንድታሳድግ ጌታ እንዲረዳት የእርሷ ቋሚ ጸሎት ነበር።4

ማስታወሻዎች

  1. ሄንሪ ቢ. አይሪን፣ “A Living Testimony,” Ensign or Liahona, May 2011, 128.

  2. ኩዌንቲን ኤል. ኩክ፣ “Let There Be Light!” Ensign ወይም Liahona፣ ህዳር 2010፣ 30።

  3. Daughters in My Kingdom: The History and Work of Relief Society (2011)፣ 163–64 ተመልከቱ።

  4. Daughters in My Kingdom፣ 164 ተመልከቱ።

ምን ማድረግ እችላለሁ?

  1. ዛሬ ለአለም ብርሀን መሆን ምን ማለት እንደሆነ ተወያዩ።

  2. የክርስቶስን ብርሀን መከተል በመከራ ውስጥ ለመጽናት እንዴት እንደሚረዳችሁ አሰላስሉ።

አትም