2010 (እ.አ.አ)
የግል ራዕይን መፈለግ እና መቀበል
ኤፕረል 2010


የሴቶች የቤት ለቤት ማስተማሪያ መልእክት፣ ሚያዝያ 2010 (እ.አ.አ)

የግል ራዕይን መፈለግ እና መቀበል

እነዚህን ቅዱስ መጻህፍትን እና ጥቅሶችን ወይም፣ አስፈላጊም ከሆነ፣ የምትጎበኗቸውን እህቶች ፍላጎት የሚያሟሉትን ሌሎች መሰረቶች አስተምሩ። ስለትምህርቱም ምስክራችሁን ስጡ። የምትጎብኟቸውንም የተማሩትን እና የሚሰማቸውን እንዲካፈሉ ጋብዟቸው።

የግል ራዕይን እንዴት መፈለግ እችላለሁ?

“የግል ራዕይን ለመቀበል ልክ ነብያት እንደሚያደርጉት፣ ቅዱስ መጻህፍትን በማጥናት፣ በመጾም፣ በመጸለይ፣ እና እምነትን በመገንባት፣ እንዘጋጃለን። እምነት ዋና ነው። ለመጀመሪያው ራዕይ ጆሴፍ የተዘጋጀበትን አስታውሱ፧

“‘ከእናንተ ግን ማንም ጥበብ ቢጎድለው …እግዚአብሔርን ይለምን፥ …

“ነገር ግን በምንም ሳይጠራጠር በእምነት ይለምን።’”1

የአስራ ሑለቱ ሐዋሪያት ቡድን አባል ካህን ሮበርት ዲ ሔልስ።

ጸሎት የእናንተ የግል የሰማይ ቁልፍ ነው። የቁልፍ መክፈቻውም በናንተ በኩል በሚገኘው መጋረጃ ላይ ነው።

“ነገር ግን ይህ ብቻ አይደለም። ራዕይ ያለምንም ጥረት እንደሚፈስ ስላሰበው፣ ጌታ አለ፧

“‘አልተረዳህም፤ በደንብ ሳታስብ እኔን ከመጠይቅህ ባሻገር እንደምሰጥህ ገምተህ ነበር።

ነገር ግን እነሆ፣ እንዲህ እልሃለሁ፣ በአእምሮህ ውስጥ ልታጠናው ይገባል፣ ከዛም ትክክለኛ መሆኑን ልትጠይቀኝ ይገባል እናም ትክክለኛ ከሆነ በውስጥህ ደረትህ እንዲቃጠል አደርጋለሁ፤ ስለዚህ ትክክል እንደሆነ ይሰማሃል።’”2

ፕሬዘደንት ቦይድ ኬ ፓከር፣ የአስራ ሑለት ሐዋሪያት ቡድን ፕሬዘደንት።

የግል ራዕይ እንዴት መቀበል እችላለሁ?

“በሚታወቀው አይነት፣ ራእይ ወይም መነሳሻ የሚመጣው ወደ ዓዕምሮ በሚመጣው ቃል ወይም ሀሳብ፣ (ኢኖስ 1፧10ንትምህርት እና ቃል ኪዳን 8፧2–3ን ተመልከቱ) በድንገት መረዳት (see ትምህርት እና ቃል ኪዳን 6፧14–15) ፣ ድርጊቶችን ለማከናወን ስለቀረበ የጥሩ ወይም መጥፎ ስሜታ፣ ወይም በድራማ አይነት አነሳሽ ጨዋታዎች ነው። የአስራ ሁለት ሐዋሪያት ቡድን ፕሬዘደንት የሆኑት ፕሬዘደንት ቦይድ ኬ ፓከር እንዳሉት፣ ‘በመነሳሳት የሚመጣው እንደ ድምጽ ሳይሆን እንደ ስሜታ ነው።’”3

የአስራ ሑለት ሐዋሪያት ቡድን አባል ካህን ዳለን ኤች ኦክስ።

“ቤተመቅደስ የመማሪያ ቤት ነው። ብዙው በቤተመቅደስ ውስጥ የሚሰጠው ትምህርት ምሳሌአዊ እና በመንፈስ የምንማረው ነው። ይህም ማለት ከበላይ እንማራለን ማለት ነው። … ወደ ቤተመቅደስ ስለዘለአለም እውነት የሚያስተምሩትን በመማር እና በማሰላሰል ጸባይ በየጊዜው ስንሄድ ስለስነ ስርዓቶች እና ቃል ኪዳኖች ትርጉሞች የሚገቡን ይጨምራሉ። … ወደቤተክርስትያን በየጊዜው ስንሄድ የምንቀበለውን የመንፈስ ጥንካሬን እና ራዕይን እንደሰትባቸው።”4

ስልቪያ ኤች ኦልረድ፣ የሴቶች መረዳጃ ማህበር አጠቃላይ አመራር የመጀመሪያ አማካሪ።

ማስታወሻዎች

  1. “Personal Revelation: The Teachings and Examples of the Prophets,” Liahona, ህዳር 2007, 88።

  2. “Personal Revelation: The Gift, the Test, and the Promise,” Ensign, ህዳር 1994, 59–60።

  3. “Eight Reasons for Revelation,” Liahona, መስከረም 2004, 8።

  4. “Holy Temples, Sacred Covenants,” Liahona, ህዳር 2008, 113, 114።

ለሴቶች የቤት ለቤት አስተማሪ እርዳታዎች

እንደ ሴቶች የቤት ለቤት አስተማሪዎች፣ ስለእህቶቻችሁ ፍላጎት እና እንዴት እነዚያን ፍላጎቶች ለማሟላት እንደምትችሉ የመንፈስ መገፋፋትን ለመቀበል ትላላችሁ። ይህን መልእክት ስታስተምሩ፣ ትክክል በሆነበት ቦታ ላይ ለየቤት ለቤት ማስተማር የተቀበላችሁንት መነሳሻ ወይም እርዳታ ተካፈሉ።

የግል ዝግጅት

1 ሳሙኤል 3፧10

1 ነገስት 19:11–12

አልማ 5፧4626፧22

3 ኔፊ 19:19–23

ትምህርት እና ቃል ኪዳን 8፧2–39፧8–988፧63–64

አትም