2011 (እ.አ.አ)
መልሶችን በአጠቃላይ ጉባኤ ለማግኘት እችላለሁ
ሴፕቴምበር 2011


ልጆች

መልሶችን በአጠቃላይ ጉባኤ ለማግኘት እችላለሁ

ፕሬዘደንት ኡክዶርፍ እንዲህ አስተምረዋል፣ ከአጠቃላይ ጉባኤ በፊት አንዳንድ ጥያቄዎች ካሰባችሁ፣ ጌታ በአጠቃላይ ጉባኤ በነቢያቱ እና በሐዋሪያቱ በኩል ያነጋግራችኋል።

  1. እንደ ቤተሰብ እና ክፍል፣ በግለሰብም ይሁን አብራችሁ ምን መማር የሚያስፈልጓችሁን ተወያዩበት። (ለምሳሌ፥ ምስክሬን እንዴት ለማጠናከር እችላለሁ? በትምህርት ቤት ባሉኝ ችግሮች እንዴት ለመቋቋም እችላለሁ?) በወረቀት ላይ ወይም በማስታወሻችሁ ላይ ጥያቄዎቻችሁን ጻፉ።

  2. ከጉባኤው ከሳምንቶች በፊት ፣ ስለእነዚህ ጥያቄዎች ለማሰብና ለመጸለይ ትችላላችሁ።

  3. በጉባኤም ጊዜ ቨጥንቃቄ አዳምጡ (ማስታወሻ መጻፍም ይረዳል)። ከእዚያም ጌታ—በቤተክርስቲያኗ መሪዎች በኩል—እንዴት ጥያቄዎቻችሁን እንደመለሰ ጻፉ።

  4. በሌላ ወረቀት ላይ የተማራችሁትን ስታደርጉ የሚያሳይ ስዕለመሳል ትችላላችሁ።

አትም