2012 (እ.አ.አ)
በሴቶች የቤት ለቤት ጉብኝት መንከባከብ እና ማገልገል
ጃንዩወሪ 2012


የሴቶች የቤት ለቤት ማስተማሪያ መልእክቶት፣ ጥር 2012 (እ.አ.አ)

በሴቶች የቤት ለቤት ጉብኝት መንከባከብ እና ማገልገል

ይህን መዝገብ አጥኑ እና ተገቢ ከሆነ ከምትጎበኟቸው እህቶች ጋር ተወያዩት። እህቶቻችሁን ለማጠናከር እና የሴቶች መረዳጃ ማህበርን የህይወታችሁ ተሳታፊ ክፍል እንዲሆን እንዲረዳችሁ ጥያቄዎቹን ተጠቀሙባቸው።

እምነት, ቤተሰብ, እርዳታ

“ልግስና [ማለት] ከቅንነት ስሜታ በላይ ነው” ብለው የቀዳሚ አመራር የመጀመሪያ አማካሪ ፕሬዘደንት ሔንሪ ቢ አይሪንግ አስተምረዋል። “ልግስና በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እምነት የሚመጣ እና የኃጢያት ክፍያው ውጢአት ነው።”1 ለሴቶች መረዳጃ ማህበር እህቶች፣ የሴቶች ቤት ለቤት ጉብኝት በአዳኝ ያለንን እምነት የምንጠቀምበት የሚሰራበት ልግስና ለመሆን ይችላል።

በሴቶች የቤት ለቤት ጉብኝት፣ እያንዳንዷን እህት በማነጋገር፣ የወንጌል መልእክትን በመካፈል፣ እና የእርሷን እና የቤተሰቧን ፍላጎት ለማወቅ በመፈለግ እንክብካቤን እንሰጣለን። “ትኩረታችን በቁጥሮች ላይ ሳይሆን በሰዎች ላይ ሲሆን፣ የሴቶች የቤት ለቤት ጉብኝት የጌታ ስራ ይሆናል” ብለው የሴቶች መረዳጃ ማህበር አጠቃላይ ፕሬዘደንት ጁሊ ቢ. ቤክ ገልጸዋል። “በእርግጥም፣ የሴቶች የቤት ለቤት ጉብኝት በምንም የሚፈጸም አይደለም። የስራ ሀላፊነት ሳይሆን በህይወት የሚኖርበት ነው። እንደ ሴቶች የቤት ለቤት አስተማሪ በታማኝነት ማገልገል የደቀ መዛሙርትነታችን መረጃ ነው።”2

በመከታተል እና በጸሎት እንክብካቤን ስንሰጥ፣ እንዴት ከሁሉም በላይ ለማገልገል እና የእያንዳንዷን እህት እና ቤተሰቧን ፍላጎት ለማሟላት እንደምንችል እንማራለን። አገልግሎት መስጠት በተለያየ መነገድ መከናወን ይቻላል—አንዳንዶቹ ታላቅ ሲሆኑ ሌሎቹም እስከዚህም ታላቅ አይደሉም። “ብዙ ጊዜ ሌላን ከፍ ለማድረግ እና ለመባረክ የሚያስፈልገው ትትንሽ የአገልግሎት ስራዎች ናቸው፥ እነዚህም ስለቤተሰብ የሚያስብ ጥያቄን መጠየቅ፣ የሚያበረታታ ቃላቶችመናገር፣ ከልብ የሚመጣ ምስጋና ማቅረብ፣ የምስጋና ካርድ መስጠት፣ በስልክ ማነጋገር ናቸው፣” ብለው ፕሬዘደንት ቶማስ ኤስ ሞንሰን አስተምረዋል። “የምንመለከት እና የምናውቅ ከሆንን፣ እና በምንነሳሳበት ነገሮች የምንሰራ ከሆንን፣ ብዙ መልካም ነገሮችን ለማከናወን እንችላለን። … በሴቶች መረዳጃ ማህበር የሴቶች የቤት ለቤት አስተማሪዎች የሚያቀርቡት የአገልግሎት ስራ መቆጠር የማይቻል ነው።”3

ከቅዱሳት መጻህፍት

ዮሀንስ 13፥15፣ 34–3521፥15ሞዛያ 2፥17ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 81፥5ሙሴ 1፥39

ከታሪካችን

በ1843 (እ.አ.አ) ፣ በናቩ ኢለኖይ የነበሩ የቤተክርስቲያኗ አባላት በአራት ዎርዶች ተከፋፈሉ። በእዚያ አመት በሐምሌ ውስጥ፣ የሴቶች መረዳጃ ማህበር መሪዎች በእያንዳንዱ ዎርድ በሴቶች የቤት ለቤት ጉብኝት ኮሚቴ ውስጥ አራት እህቶችን መደቡ። የሴቶች የቤት ለቤት ጉብኝት ኮሚቴ ሀላፊነትም በተጨማሪ የእርዳታ ፍላጎቶችን ለመመልከት እና መፅዋዕትን መሰብሰብ ነበሩ። የሴቶች መረዳጃ ማህበር እነዚህን መፅዋዕቶችን እርዳታ የሚፈልጉትን ለመርዳት ተጠቀሙበት።4

ምንም እንኳን የሴቶች የቤት ለቤት አስተማሪዎች መፅዋዕትን አሁን የማይሰበስቡ ቢሆኑም፣ መንፈሳዊ እና ጊዜአዊ እርዳታ የሚያስፈልገውን የማወቅ እና እነዚህን ፍላጎቶች ለማሟላት የመስራት ሀላፊነት አለባቸው። ሁለተኛ የሴቶች መረዳጃ ማህበር አጠቃላይ ፕሬዘደንት የነበሩት እላይዛ አር. ስኖው እንደገለጹት፥ “አስተማሪ… ወደ ቤት ውስጥ ስትገባ ምን አይነት መንፈስ እንዳለ ለማወቅ የጌታ መንፈስ በብዛት እንዲኖራት በእርግጥም ያስፈልጋታል። … በቤት ውስጥ የሚገኘውን መንፈስ ለማወቅ… እናየሰላም እና የመፅናኛ ቃላትን ለመናገር፣ በእግዚአብሔር እና በመንፈስ ቅዱስ ፊት [መንፈስን] ለማግኘት ለምኑ፣ እናም የበረዳት እህት ካገኛችሁ፣ በእቅፋችሁ ልጆችን እንደምታደርጉት በልባችሁ አስገቧት እናም ሙቀት ስጧት።”5

ማስታወሻዎች

  1. ሔንሪ ቢ አይሪንግ፣ “The Enduring Legacy of Relief Society፣” Liahona, ህዳር 2009፣ 121።

  2. ጁሊ ቢ ቤክ፣ “Relief Society: A Sacred Work፣” Liahona ህዳር 2009፣ 114።

  3. ቶማስ ኤስ ሞንሰን፣ “Three Goals to Guide You፣” Liahona ህዳር 2007፣ 120–21።

  4. Daughters in My Kingdom: The History and Work of Relief Society (2011)፣ 105 ተመልከቱ።

  5. እላይዛ አር. ስኖው፣ Daughters in My Kingdom ውስጥ፣ 108።

ምን ማድረግ እችላለሁ?

  1. እህቶቼ የማፈቅራቸው እና የማስብባቸው ጉደኛቸው እንደሆንኩኝ እንዲሰማቸው ምን አደርጋለሁ?

  2. ሌሎችን ለመንከባከብ የተሻለ ለመሆን ምን ማግረግ እችላለሁ?

አትም