2015 (እ.አ.አ)
የኢየሱስ ክርስቶስ መለኮታዊ ባህሪ፥ መልካምነት
ጁን 2015


የሴቶች የቤት ለቤት ጉብኝት መልእክት ሰኔ 2015 (እ.አ.አ)

የኢየሱስ ክርስቶስ መለኮታዊ ባህሪ፥ መልካምነት

በጸሎት መንፈስ ይህንን መረጃ አንብቡት እና ምን እንደምታካፍሉ ለማወቅ እሹ። የአዳኝን ህይወት እና ተልእኮ መረዳት በእርሱ ያላችሁን እምነት የሚያሳድገው እና በሴቶች የቤት ለቤት ትምህርት ምክንያት የምትንከባከቧቸውን የሚባርከው እንዴት ነው? ለተጨማሪ መረጃ ወደreliefsociety.lds.org ሂዱ።

እምነት፣ ቤተሰብ፣ እርዳታ

“አንጀትህም ለሁሉም ሰው እና ለእምነት ቤተ ሰዎች በልግስና ይሞላ፣ እና ምግባረ በጎነትም ሳያቋርጥ አስተሳሰብህን ያሳምር፤ ከዚያም ልበ ሙሉነትህ በእግዚአብሔር ፊት እየጠነከረ ይሄዳል፤ እና የክህነት ትምህርትም በነፍስህ ላይ እንደ ሰማይ ጠል ትንጠባጠብልሀለች።”(ት እና ቃ 121፥45)።

መልካምነት ምንድን ነው? ፕሬዘደንት ጀምስ ኢ ፋውስት [1920–2007 (እ.አ.አ)] እንደዚህ አሉ፥ “መልካምነት በሙሉ ትርጉሙ ስነ-ምግባራችንን ለመቅረፅ የሚረዳ የፅድቅን ባህሪያት ሁሉ ያጠቃልላል።”1ፕሬዘደንት ጎረርደን ቢ ሒንክሊ [1910–2008 (እ.አ.አ)] እንደዚህ በማለት ጨመሩ፥ “የእግዚአብሔር ፍቅር የሁሉም ጥሩነት፣ የሁሉም መልካምነት፣ የሁሉም የስነ-ምግባር ጥንካሬ ስር ነው።”2

በሴቶች እና በመልካምነት መሃል ስላለው ግንኙነትም፣ የአስራሁለት ሐዋርያት ምልአተ ጉባኤ አባል ሽማግሌ ዲ ታድ ክርስቶፈርሰን እንደዚህ አሉ፥ “ሴቶች ከራሳቸው ጋር የተወሰነ መልካምነት፣ እንዲሁም በግንኙነትና በባህል ውስጥ እምነት፣ ድፍረት፣ ሩህሩህነት እና ብልጽግና አይነት ውጤታዎችን የሚያመጡበት፣ መለኮታዊ ስጦታ ወደ አለም ይዘው ይመጣሉ። …

“እህቶች፣ ከግንኙነቶቻችሁ ሁሉ፣ የስነ-ምግባራችሁ ኃይል ምንጭ ከሆነው ከሰማይ አባታችሁ ከእግዚአብሔር ጋር ያላችሁን ግንኙነት ነው በሕይወታችሁ ውስጥ ቅድሚያ መስጠት የሚገባችሁ። የኢየሱስ ኃይል ለአባቱ ፈቃድ ባለው ብቸኛ ፍቅር አማካኝነት እንደመጣ አስታውሱ። … የአብ እና የወልድ እንደዛ አይነት ደቀመዝሙር ለመሆን ጣሩ፣ እና ተፅኖአችሁ መቼም አይደበዝዝም።”3

ተጨማሪ ጥቅሶች

መዝሙረ ዳዊት 24፥3–5ፊልጵስዩስ 4፥82 ጴጥሮስ 1፥3–5አልማ 31፥5ት እና ቃ 38፥23–24

ከቅዱሳት መጻህፍት

ዛሬ፣ መልካም ሴቶች በእምነት ተሞልተው ወደ አዳኙ ይቀርባሉ። በሉቃስ 8 ውስጥ ለ12 አመታት ሊድን ያልቻለ የደም ችግር ስላለባት ሴት እናነባለን። “ከ[ክርስቶስ] ጀርባ ስትመጣ” ፈውስ ፈለገች “እና የቀሚሱን ጫፍ ነካችው እና ወዲያው የደም ችግሯ [ቆመ]።“ኢየሱስም አንድ ሰው ዳስሶኛል፥ ኃይል ከእኔ እንደ ወጣ እኔ አውቃለሁና አለ።”4 ይህቺ መልካም ሴት ከፊቱ ወድቃ ለእርሱም “በሕዝቡ ፊት” “ነክታው” እና “እንደተፈወሰች” አወጀች። እርሱም ልጄ ሆይ እምነትሽ አድኖሻል በሰላም ሂጂ አላት”(ሉቃስ 8፥43–48፤ እንዲሁም 6፥17–19 ተመልከቱ)።

በመልካምነቱ አማካኝነት፣5 ወደ እርሱ በድፍረት እና በእምነት ለመምጣት ስንመርጥ፣ ክርስቶስም ለመፈወስ፣ ለማስቻል፣ ለማጠንከር፣ ለማፅናናት እና ለማስደሰት ይችላል።

ማስታወሻዎች

  1. ጀምስ ኢ ፋውስት፣ “The Virtues of Righteous Daughters of God፣” Liahona፣ግንቦት 2003 (እ.አ.አ)፣ 108።

  2. ጎርደን ቢ. ሒንክሊ፣ “Excerpts from Recent Addresses of President Gordon B. Hinckley፣” Ensign፣ሚያዚያ 1996 (እ.አ.አ)፣ 73።

  3. ዲ. ታድ ክርስቶፈርሰን፣ “The Moral Force of Women፣” Liahona፣ህዳር 2013 (እ.አ.አ)፣ 29፣ 31።

  4. ጥሩነት ኃይል አለው (ማርቆስ 5፥30 ተመልከቱ)።

  5. በቅዱሳት መጽሐፍ መመሪያ ውስጥ፣ “ክህነት” እንደሚቀጥለው ተተርጉሟል “ለሰው ደህንነት በሁሉም ነገሮች ሰዎች ለመስራት እንዲችሉ እግዚአብሔር ለሰው የሚሰጠው ስልጣን እና ሀይል” (ት እና ቃ 50፥26–27)።

ይህን አስቡበት

ጥሩነት እንዴት ኃይል ይሰጠናል እና ያጠናክረናን?

አትም