2021 (እ.አ.አ)
ኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስትያኑን ሰየመ
ጥቅምት 2021 (እ.አ.አ)


“ኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስትያኑን ሰየመ፣” ጓደኛ ጥቅምት 2021 (እ.አ.አ)።

ወርሃዊ የጓደኛ መልእክት፣ ጥቅምት 2021 (እ.አ.አ)

ኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስትያኑን ሰየመ

ምስል
ኢየሱስ ክርስቶስ
ምስል
ጆሴፍ ስሚዝ

ኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስትያኗን ምን ብሎ መሰየም እንዳለበት ለጆሴፍ ስሚዝ ነገረው። “የኋላኛው ቀን ቅዱሳን የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስትያን“ ተብላ ትጠራለች አለው።

ምስል
የቤተክርስትያን የመሰብሰቢያ አዳራሽ

ኢየሱስ ክርስቶስ የሚሉት ቃላት ከቤተክርስትያና ስም እጅግ አስፈላጊው ክፍል ነው። ይህችም የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በመሆኗ፣ በእርሱ ስም ተሰይማለች።

ምስል
ህጻናት የመፅሐፈ ሞርሞንን ቅጂዎች ይዘው

የኋላኛው ቀን ቅዱሳን ማለት የዚህ ዘመን የቤተክርስትያን አባላት ማለት ነው።

ምስል
ሴቶች እና ህጻናት አጠቃላይ ጉባኤን እየተመለከቱ

ነቢያት እና ሐዋርያት የቤተክርስትያኗን ትክክለኛ ስም መጠቀም አስፈላጊ እንደሆነ አስተምረዋል። በኢየሱስ ክርስቶስ እንደምናምን ሌሎች እንዲያውቁ ይረዳል።

ምስል
ህጻናት የኢየሱስ ክርስቶስን ስእል እየተመለከቱ

ሌሎች በምን እንደማምን ሲጠይቁኝ፣ “በኢየሱስ ክርስቶስ አምናለሁ። እኔ የኋለኛው ቀን ቅዱሳን የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አባል ነኝ” ብዬ መመለስ እችላለሁ።

የሚቀባ ገፅ

በኢየሱስ ክርስቶስ አምናለሁ

ምስል
ህጻናት የኢየሱስ ክርስቶስን ምስል ይዘው

ለማውረድ ስዕሉ ላይ ጠቅ ያድርጉ።

ስእል በኤፕረል ስቶት

ስለ ኢየሱስ እንድትማሩ ምን ይረዳችኋል?

አትም