አዲስ ኪዳን 2023 (እ.አ.አ)
ሚያዝያ 3–9 (እ.አ.አ) ትንሳኤ፦ “መቃብር ሆይ፣ ድል መንሣትህ የት አለ?”


“ሚያዝያ 3–9 (እ.አ.አ)። ትንሳኤ፤ ‘መቃብር ሆይ፣ ድል መንሳትህ የት አለ’” ኑ፣ ተከተሉኝ—ለግለሰቦች እና ለቤተሰቦች፦ አዲስ ኪዳን 2023 (እ.አ.አ) 2022 (እ.አ.አ)

“ሚያዝያ 3–9 (እ.አ.አ)። ትንሳኤ፤ ኑ፣ ተከተሉኝ—ለግለሰቦች እና ለቤተሰቦች፦ 2023 (እ.አ.አ)

ምስል
የአትክልት ስፍራ መቃብር

ሚያዝያ 3–9 (እ.አ.አ)

ትንሳኤ

“መቃብር ሆይ፣ ድል መንሣትህ የት አለ?”

በዚህ ረቂቅ ላይ ስለ አዳኙ ትንሳኤ ምስክርነቶችን ስታነቡ ከመንፈስ ቅዱስ ለሚመጡ ስሜቶች ትኩረት ስጡ።

ያሳደረባችሁን ስሜት መዝግቡ

በአዳኙ ህይወት የመጨረሻ ሳምንት ላይ በእርሱ ዙርያ ያሉ ብዙ አይሁዶች በፋሲካ በአል ላይ ይሳተፉ ነበር። የእስራኤልን ቤት ከግብጽ ባርነት ነጻ መውጣት ለማስታወስ በአንድነት በመሰብሰብ ምግብ ያዘጋጃሉ፣ ሙዚቃ ይጫወታሉ። በጠቦት ደም በራቸው ላይ ምልክት ያደረጉ ቅድመ አያቶቻቸውን ቤት አጥፊው መልአክ ያለፈበትን ታሪክ ቤተሰቦች ይሰማሉ። በአንጻራዊው በነጻ መውጣት ምልክቶች በተሞላው በዓል ላይ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ የእግዚአብሔር በግ በስቃዩ፣ በሞቱ እና በትንሳኤው ከሃጢያት እና ሞት ነጻ ሊያወጣቸው እንደነበር የሚያውቁት ጥቂት ሰዎች ነበሩ። ቢሆንም ኢየሱስን፥ ቃል የተገባለትን መሲህ፥ የዘላለም አዳኛቸውን ያወቁት ነበሩ። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀመዛሙርት “ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም…፤ በሦስተኛው ቀን ተነሣ” (1 ቆሮንቶስ 15፥3–4) በማለት ለአለም ሁሉ መሰከሩ።

ምስል
የግል ጥናት ምልክት

ለግል የቅዱሳት መጻህፍት ጥናት ሃሳቦች

ማቴዎስ 21–28

ኢየሱስ ክርስቶስ ከሃጢያት እና ሞት ያድነኛል፣ በድካሜ ያበረታኛል፤ በፈተናዎቼ ያጽናናኛል።

በዚህ ሳምንት በአዳኙ የሃጢያት ክፍያ በረከቶች ላይ ማተኮርያ አንዱ መንገድ ስለ አዳኙ ህይወት የመጨረሻ ሳምንት በየቀኑ በማንበብ ጊዜ በማሳለፍ ነው። የአዳኙ ፍቅር እንዲሰማችሁ በእነዚህ ቁጥሮች ላይ የሚረዳችሁን ምን ታገኛላችሁ? እነዚህ ምዕራፎች እርሱ ከሃጢያት፣ ከሞት፣ ከፈተና እና ከድካም እንዴት እንደሚያድናችሁ የሚያስተምራችሁን አሰላስሉ። በማዳን ሃይሉ ላይ እምነታችሁን እንዴት እየተለማመዳችሁ ነው?

በተጨማሪም Easter.ComeuntoChrist.orgን ተመልከቱ።

ምስል
ክርስቶስ በመስቀል ላይ

ስቅለት፣ በሉዊስ ፓርከር

ማቴዎስ 28፥1–10ሉቃስ 24፥13–35ዮሐንስ 20፥19–291 ቆሮንቶስ 15፥1–8፣ 55

ብዙ የአይን እማኞች ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ መስክረዋል።

ክርስቶስ ላይ ሲያሾፉ፣ ሲበድሉት እና ሲሰቅሉት ደቀመዝቅሙርቱ ሲመለከቱት ምን ተሰምቷቸው ሊሆን እንደሚችል ገምቱ። ሃይሉን ተመልክተዋል፣ የአስተምሮቱን እውነተኛነት ተሰምቷቸዋል እና የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነም እምነት ነበራቸው። ሞቱን መመልከት ደቀመዛሙርቱ ከባድ ሃዘን እና ግራ መጋባት እንዲሰማቸው አድርጎ ይሆናል። ነገር ግን ብዙም ሳይርቅ የእርሱን ትንሳኤ ታላቅ ተአምር ምስክር ሆኑ።

ትንሳኤ ያደረገውን አዳኝ ከተመለከቱ ሰዎች ጽሁፍ ምን ትማራላችሁ? በማቴዎስ 28፥1–10ሉቃስ 24፥13–35ዮሐንስ 20፥19–29፤ እና 1 ቆሮንቶስ 15፥1–8፣ 55፣ ላይ የእያንዳንዱን ሰው ገጠመኝ ምልክት አድርጉ ወይም ልብ በሉ። (ትንሳኤ ያደረገው ክርስቶስ ሌሎች ምስክሮች በ3 ኔፊ 11ሞርሞን 1፥15ኤተር 12፥38–39ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 76፥19–24110፥1–10፤ እና የጆሴፍ ስሚዝ—ታሪክ 1፥15–17፣ ላይ ይገኛሉ።) ስለ እነዚህ ምስክሮች የሚያስደንቃችሁ ምስክርነት ምንድነው? ከትንሳኤው በኋላ ሌሎችም ከሞት ተነስተው ለብዙዎች ታይተው ነበር (ማቴዎስ 27፥52–533 ኔፊ 23፥9ን ተመልከቱ)። በአዳኙ ላይ ያላችሁ እምነት እና የትንሳኤ ቃልኪዳን በአኗኗራችሁ ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድረው እንዴት ነው?

በተጨማሪም “ኢየሱስ ትንሳኤ አድርጓል” “የተነሳው ጌታ ለሐዋርያት ታየ” “ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው” (ቪድዮ)፣ ChurchofJesusChrist.org፣ ላይ ተመልከቱ።

1 ጴጥሮስ 1፥3–11

ኢየሱስ ክርስቶስ ተስፋ እና ደስታን ይሰጠኛል።

1 ጴጥሮስ 1፥3–11 ላይ ያሉ የትኞቹ ቃላት ወይም ሃረጎች በኢየሱስ ክርስቶስ ተስፋ ይሰጧችኋል? ይህ ተስፋ መች ተሰምቷችሁ ያውቃል?

ሽማግሌ ጋሬት ደብሊው. ጎንግ ትንሳኤ “እግሮቻቸውን ላጡ፣ ማየት፣ መስማት ወይም መራመድ ለተሳናቸው፣ ለከባድ በሽታ፣ ለአእምሮ ህመም ወይም ሌላ አቅማቸው ለተዳከሙ ሰዎች ተስፋ ይሰጣል። ያገኘናል። ሙሉም ያደርገናል። … [ደግሞም] ‘እግዚአብሔር እራሱ ለአለም ሃጢያቶች የሃጢያት ክፍያ [ይከፍላል]’ [አልማ 42፥15]፣… በምህረት እርሱ በድካማችን ይረዳናል።… ንስሀ እንገባለን እናም የምንችለውን ሁሉ እናደርጋለን። በዘላለም ‘ፍቅር ክንዶች [ይከበናል]’ [2 ኔፊ 1፥15]” በማለት መስክሯል (“ሆሳና እና ሃሌሉያ—ህያው የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ፤ የዳግም መመለስ እና ትንሳኤ ማዕከል፣” ሊያሆና፣ ግንቦት 2020 (እ.አ.አ) 54)።

በተጨማሪም አልማ 27፥2836፥1–243 ኔፊ 9፥11–17ሞሮኒ 7፥40–41ን ተመልከቱ።

ምስል
የቤተሰብ ጥናት ምልክት

ለቤተሰብ ቅዱሳት መጻህፍት ጥናትና ለቤተሰብ የቤት ምሽት ሃሳቦች

ComeuntoChrist.orgEaster.ComeuntoChrist.org በአዳኙ ህይወት የመጨረሻ ሳምንት በእያንዳንዱ ቀን የተከናወኑ ክስተቶችን የጊዜ ሰሌዳ እና ማብራርያ ይዟል። በሳምንቱ እያንዳንዱ ቀን ቤተሰባችሁ አዳኙ በዚያች ቀን ምን እንዳደረገ ለማወቅ እነዚህን ማብራርያዎች መከለስ ይችላል ወይም ስለ እሱ የመጨረሻ ሳምንት እንደ ቤተሰብ ማንበብ ትችላላችሁ (የሚመከር ዝርዝር በ“ለግል የቅዱስ መጽሃፍ ጥናት ሃሳቦች” ላይ ከላይ ተመልከቱ)።

መዝሙር እና የልጆች መዝሙር መጽሐፍበዚህ ሳምንት ስለ አዳኙ የሃጢያት ክፍያ እና ትንሳኤ መዝሙር፥ በአንድነት ልትዘምሩ ትችላላችሁ፤ ለእናንተ ያልተለመዱ የሆኑትን ጨምሮ። (የመዝሙሮች ወይም የልጆች መዝሙር መጽሐፍ፣ የርዕስ ማውጫ በእነዚህ ርዕሶች ተመልከቱ፤ “የሃጥያት ክፍያ”፣ “ትንሳኤ” ወይም “ከሞት መነሳት።”) የቤተሰብ አባላት መዝሙሮቹን እንዲለምዱ ከቃላቱ ጋር የሚሄዱ ስዕሎችን ማሳየት ትችላላችሁ።

“ኢየሱስ ክርስቶስ” ስብስብ በወንጌል ላይብረሪ።ኢየሱስ ክርስቶስ” የሚል ርዕስ ያለው የወንጌል ላይብረሪ ስብስብ በዚህ ትንሳኤ የአዳኙን ከሞት መነሳት ለማክበር ቪድዮዎችን፣ የጥበብ ስራዎችን እና ሙዚቃዎችን ይዟል።

“ህያው ክርስቶስ፥ የሐዋሪያት ምስክርነት”እንደ ቤተሰብ “ህያው ክርስቶስ፥ የሐዋሪያት ምስክርነት” (ChurchofJesusChrist.org)ን አንብቡ። ከዚህ ምስክርነት እያንዳንዱ የቤተሰብ አባል የትንሳኤ መልዕክት እንዲመርጡ እና እንዲያካፍሉ ጋብዟቸው። ለምሳሌ፣ በማህበራዊ ሚድያ፣ በፊት ለፊት በራችሁ ወይም በቤታችሁ እንዲታይ የሚለጠፍ ስዕል ማዘጋጀት ትችላላችሁ።

ልጆችን ለማስተማር ተጨማሪ ሃሳቦችን ለማግኘት የዚህን ሳምንት ዝርዝርኑ፣ ተከተሉኝ—ለመጀመሪያ ክፍልን ይመልከቱ።

የሚመከር መዝሙር፦ “ኢየሱስ ተነስቷል፣” የልጆች መዝሙር መጽሃፍ፣70።

የግል ጥናትን ማሻሻል

ማሳካት የምትችሉትን ግቦች አስቅምጡ። ጥቂት ደቂቃዎችንም ቢሆን ቅዱሳት መጻህፍትን በማንበብ ማሳለፍ ህይወታችሁን ሊባርክ ይችላል። በየቀኑ ለማጥናት አስቡ፣ ራሳችሁን ይህን የምታስታውሱበትን መንገድ አግኙ፣ ለመከተል የተቻላችሁን ሁሉ አድርጉ። ብትረሱ እንኳን ተስፋ አትቁረጡ። እንደገና ጀምሩ።

ምስል
ክርስቶስ በጌቴሴማኒ

በጌቴሴማኒ፣ በአደም አብራም

አትም