አዲስ ኪዳን 2023 (እ.አ.አ)
መስከረም 4–10 (እ.አ.አ) 1 ቆሮንቶስ 14–16፦ “እግዚአብሔር የሰላም አምላክ ነው እንጂ የሁከት አምላክ አይደለም”


“መስከረም 4–10 (እ.አ.አ) 1 ቆሮንቶስ 14–16፦ ‘እግዚአብሔር የሰላም አምላክ ነው እንጂ የሁከት አምላክ አይደለም’” ኑ፣ ተከተሉኝ—ለግለሰቦች እና ለቤተሰቦች፦ አዲስ ኪዳን 2023 (እ.አ.አ) [2022 (እ.አ.አ)]

“መስከረም 4–10 (እ.አ.አ) 1 ቆሮንቶስ 14–16፣” ኑ፣ ተከተሉኝ—ለግለሰቦች እና ለቤተሰቦች፦ 2023 (እ.አ.አ)

ምስል
የቤተመቅደስ ማጥመቂያ ገንዳ

መስከረም 4–10 (እ.አ.አ)

1 ቆሮንቶስ 14–16

“እግዚአብሔር የሰላም አምላክ ነው እንጂ የሁከት አምላክ አይደለም”

1 ቆሮንቶስ 14–16ን በምታነቡበት ጊዜ ግንዛቤዎቻችሁን መዝግቡ። መንፈስ ስላስተማራችሁ ነገር ጸልዩ፣ እናም እናንተ ተጨማሪ እንድትማሩ የሚፈልገው ነገር ካለ የሰማይ አባትን ጠይቁ።

ያሳደረባችሁን ስሜት መዝግቡ

በቆሮንቶስ ቤተክርስቲያኗ እና ትምህርቶቿ በአንጻሩ አዲስ ስለነበሩ፣ የቆሮንቶስ ቅዱሳን ግራ መጋባት አጋጥሟቸው እንደነበረ መረዳት ይቻላል። ጳውሎስ ቀደም ሲል የወንጌልን መሠረታዊ እውነት “ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥ … እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሣ” (1 ቆሮንቶስ 15፥3–4) በማለት አስተምሯቸዋል። ነገር ግን ብዙም ሳይቆይ አንዳንድ አባላት “ትንሣኤ ሙታን የለም” (1 ቆሮንቶስ 15፥12) እያሉ ማስተማር ጀመሩ። ጳውሎስ የተማሩትን እውነት “[እንዲያስቡ]” (1 ቆሮንቶስ 15፥2) ተማጸናቸው። በወንጌል እውነቶች ላይ እርስ በርስ የሚጋጩ የሚመስሉ አስተያየቶች ሲያጋጥሙን “እግዚአብሔርስ የሰላም አምላክ ነው እንጂ የሁከት አምላክ አይደለም” (1ቆሮንቶስ 14፥33) የሚለውን ማስታወስ ጥሩ ነው። የጌታን የተሾሙ አገልጋዮችን ማዳመጥ እና በተደጋጋሚ የሚያስተምሩትን ቀላል እውነቶች መያዛችን ሰላምን እንድናገኝ እና “በሃይማኖት [እንድንቆም]” (1 ቆሮንቶስ 16፥13) ይረዳናል።

ምስል
የግል ጥናት ምልክት

ለግል የቅዱሳት መጻህፍት ጥናት ሃሳቦች

1 ቆሮንቶስ 14

የትንቢትን ስጦታ መፈለግ እችላለሁ።

የትንቢት ስጦታ ምንድነው? የወደፊቱን የመተንበይ ችሎታ ነው? ለነቢያት ብቻ ነው? ወይም ይህን ስጦታ ማንም ሊቀበል ይችላል?

1 ቆሮንቶስ 14፥3፣ 31፣ 39–40ን ስታጠኑ እነዚህን ጥያቄዎች አሰላስሉ። በተጨማሪም ራዕይ 19፥10 እና በቅዱሳት መጻህፍት መመርያ ላይ “ትንቢት” (scriptures.ChurchofJesusChrist.org) አንብቡ። በተማራችሁት መሠረት የትንቢት ስጦታን እንዴት ትገልጻላችሁ? ጳውሎስ ቆሮንቶስን “ትንቢት ለመናገር በብርቱ ፈልጉ” በማለት ሲጋብዝ ምን ማለቱ ሊሆን ይችላል? (1 ቆሮንቶስ 14፥39)። ይህንን ግብዣ እንዴት መቀበል ትችላላችሁ?

በተጨማሪም ኢዮኤል 2፥28–29አልማ 17፥3ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 11፥23–28ን ተመልከቱ።

1 ቆሮንቶስ 14፥34–35

በእነዚህ ጥቅሶች ውስጥ ስለ ሴቶች ያለው መግለጫ ዛሬ እንዴት ይሠራል?

በጳውሎስ ዘመን ሴቶች በቤተክርስቲያኗ ስብሰባዎች ውስጥ ጨምሮ በማህበረሰቡ ውስጥ እንዴት መሳተፍ እንዳለባቸው የተለያዩ አመለካከቶች ነበሩ። በጳውሎስ ዘመን በ1 ቆሮንቶስ 14፥34–35 ላይ ያለው አስተምሮት ምንም ቢሆን ምን፣ ዛሬ በቤተክርስቲያን ውስጥ ሴቶች መናገር እና መምራት እንደሌለባቸው እየተናገረ እንደሆነ መረዳት አይገባም (ጆሴፍ ስሚዝ ትርጉም፣ 1 ቆሮንቶስ 14፥34 [በ1 ቆሮንቶስ 14፥34፣ የግርጌ ማስታወሻ ] ላይ ተመልከቱ)። ፕሬዘደንት ረስል ኤም. ኔልሰን ዛሬ ለቤተክርስቲያኗ ሴቶች “እኛ… ጥንካሬያችሁን፣ መለወጣችሁን፣ ጽኑ እምነታችሁን፣ የመምራት ችሎታችሁን፣ ጥበባችሁን እና ድምጻችሁን እንፈልጋለን። ቅዱስ ቃልኪዳኖችን የሚገቡ፣ ከዚያም የሚጠብቁ፣ በእግዚአብሔር ሀይል እና ስልጣን መናገር የሚችሉ ሴቶች በሌሉበት የእግዚአብሔር መንግስት ሙሉ አይደልም፣ ሊሆንም አይችልም!”። (“ለእህቶቼ ልመና፣” ሊያሆና፣ ህዳር 2015 (እ.አ.አ)፣ 96)።

1 ቆሮንቶስ 15፥1–34፣ 53–58

ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አደረገ።

የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ለክርስትና በጣም መሠረታዊ ነው፣ አንድ ሰው ያለ እሱ ክርስትና የለም ሊል ይችላል፤ የጳውሎስን ቃላት ለመጠቀም፣ “እንግዲያውስ ስብከታችን ከንቱ ነው፣ እምነታችሁም ደግሞ ከንቱ ናት” (1 ቆሮንቶስ 15፥14)። ሆኖም አንዳንድ የቆሮንቶስ ቅዱሳን “ትንሣኤ ሙታን የለም” ብለው ያስተምሩ ነበር (1 ቆሮንቶስ 15፥12)። በ1 ቆሮንቶስ 15፣ ውስጥ የጳውሎስን ምላሽ በምታነቡበት ጊዜ፣ ትንሣኤን ባታምኑ ኖሮ ህይወታችሁ እንዴት የተለየ ሊሆን እንደሚችል ለማሰብ ትንሽ ጊዜ ውሰዱ (2 ኔፊ 9፥6–19አልማ 40፥19–23ትምህርት እና ቃልኪዳኖች 93፥33–34)። “ክርስቶስ ካልተነሳ እምነታችሁ ከንቱ ናት” የሚለው ሐረግ ለእናንተ ምን ማለት ነው? (ቁጥር 17)።

በተጨማሪም ጳውሎስ ለሙታን ጥምቀትን ለትንሣኤው እውነት ማስረጃ አድርጎ መጥቀሱ ልብ ሊባል የሚገባው ነው (1 ቆሮንቶስ 15፥29ን ተመልከቱ)። የቤተመቅደስ እና የቤተሰብ ታሪክ ስራ በትንሳኤ ትምህርት ላይ እምነታችሁን እንዴት አጠንክሯል?

በተጨማሪም ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 138፥11–37ን ተመልከቱ።

1 ቆሮንቶስ 15፥35–54

ከሞት የተነሱ አካላት ከሟች አካላት የተለዩ ናቸው።

የትንሣኤ አካል ምን እንደሆነ አስባችሁ ታውቃላችሁ? በ1 ቆሮንቶስ 15፥35፣ መሠረት አንዳንድ የቆሮንቶስ ሰዎች ተመሳሳይ ጥያቄ ነበራቸው። በቁጥር 36–54፣ ውስጥ የጳውሎስን መልስ አንባቡ፣ እናም በሚሞቱ አካላት እና በትንሣኤ አካላት መካከል ያለውን ልዩነት የሚገልጹ ቃላትን እና ሀረጎችን ልብ በሉ። ይህን ስታደርጉ ቁጥሮች 40–42 ን ከ ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 76፥50–112፣ ጋር ማነጻጸር ትችላላችሁ። ይህ ለነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ የመጣው መገለጥ ግንዛቤያችሁ ላይ ምን ይጨምራል? (በተጨማሪም የጆሴፍ ስሚዝ ትርጉም፣ 1 ቆሮንቶስ 15፥40 [በ1 ቆሮንቶስ 15፥40፣ የግርጌ ማስታወሻ ] ተመልከቱ)። እነዚህ እውነቶች ለእናንተ ዋጋ ያላቸው የሆኑት ለምንድን ነው?

በተጨማሪም ሉቃስ 24፥39አልማ 11፥43–45ትምህርት እና ቃልኪዳ ኦች 88፥14–33ን ተመልከቱ።

ምስል
የጸሃይ መውጫ

“የፀሐይ ክብር አንድ ነው” (1 ቆሮንቶስ 15፥41)።

ምስል
የቤተሰብ ጥናት ምልክት

ለቤተሰብ ቅዱሳት መጻህፍት ጥናትና ለቤተሰብ የቤት ምሽት ሃሳቦች

1 ቆሮንቶስ 15፥29ቁጥር 29 ልክ እንደዛሬው የጥንት ክርስቲያኖች በሙታን ጥምቀት እንደተሳተፉ እንማራለን። ለቅድመ አያቶቻችን ለምን እንደምንጠመቅ ለሌሎች እንዴት እንገልፃለን? (“የሙታን ጥምቀት ምንድነው?”) [ቪዲዮ]፣ ChurchofJesusChrist.orgን ተመልከቱ)። ለሟች ቅድመ አያቶቻችን የቤተመቅደስ ስርዓቶችን ለመፈጸም እንደ ቤተሰብ ምን እያደረግን ነው? በዚህ ርዕስ ላይ ተጨማሪ ምንጮችን በወንጌል ርዕሶች ” “ለሙታን ጥምቀት” (topics.ChurchofJesusChrist.org) እና በFamilySearch.org፣ ላይ ማግኘት ትችላላችሁ።

1 ቆሮንቶስ 15፥35–54ቤተሰባችሁ ጳውሎስ ሟች አካላት ከትንሣኤ አካላት እንዴት እንደሚለዩ የገለጸውን አንዳንድ ቃላትን እንዲረዱ ለማገዝ ምን ዓይነት ዕቃዎች ወይም ስዕሎች ልታሳዩ ትችላላችሁ? ለምሳሌ በሚበሰብሰው እና በማይበሰብሰው መካከል ያለውን ልዩነት ለማሳየት (ቁጥር 52–54ን ተመልከቱ) የዛገ ብረትን እና የማይዝግ ብረትን ማሳየት ትችላላችሁ። ወይም ደካማ ነገርን ከኃይለኛ ነገር ጋር ማነጻጸር ትችላላችሁ (ቁጥር 43ን ተመልከቱ)።

1 ቆሮንቶስ 15፥55–57ቤተሰባችሁ በህይወት የሌለን ሰው የሚያውቅ ከሆነ ስለእነዚህ ጥቅሶች የሚደረግ ውይይት ትርጉም ያለው ሊሆን ይችላል። የቤተሰብ አባላት ኢየሱስ ክርስቶስ “የሞትን መውጊያን” እንዴት እንደወሰደ ምስክርነት ሊሰጡ ይችላሉ (ቁጥር 56)።

1 ቆሮንቶስ 16፥13የቤተሰብ አባላት ከዚህ ጥቅስ ጋር እንዲዛመዱ ለማገዝ፣ መሬት ላይ ክብ መሳል እና አንድ የቤተሰብ አባል ዓይኖቹን ጨፍኖ በውስጡ “[እንዲቆም]” ማዘዝ ትችላላችሁ። ከዚያ ሌሎች እሱን ወይም እሷን ከክቡ ለመግፋት ወይም ለመሳብ ሊሞክሩ ይችላሉ። በክቡ ውስጥ ያለው ሰው ዓይኖቹ ሲከፈቱ እና “ንቁ” ሲሆኑ ምን ልዩነት አለው? መጥፎ ምርጫዎችን ለማድረግ ስንፈተን “[ጠንክረን ለመቆም]” ምን እናድርግ? (በተጨማሪ “በጀልባው ውስጥ ቆዩ እና ጠብቁ!፣” [ቪዲዮ] ChurchofJesusChrist.orgን ተመልከቱ)።

ልጆችን ለማስተማር ተጨማሪ ሃሳቦችን ለማግኘት የዚህን ሳምንት ዝርዝርኑ፣ ተከተሉኝ—ለመጀመሪያ ክፍል ተመልከቱ።

በሀሳብ የሚቀርብ መዝሙር፦ “ተነስቷል፣” መዝሙሮች፣ ቁጥር 199።

የግል ጥናትን ማሻሻል

ንድፎችን ፈልጉ። በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ጌታ ሥራውን እንዴት እንደሚሠራ የሚያሳዩ ንድፎችን እናገኛለን። በ1 ቆሮንቶስ 14 ውስጥ አንዳችን ሌላችንን እንድናንጽ የሚረዱ ምን ምሳሌዎችን ታገኛላችሁ?

ምስል
ክርስቶስ በአትክልቱ መቃብር ለማርያም ተገለጠ

ለምን ታለቅሺያለሽ፣ © ሳይመን ዴዌይ 2021 (እ.አ.አ)። ከአልተስ ፊን አርት/www.altusfineart.com፣ በፈቃድ ጥቅም ላይ ውሏል።

አትም