አዲስ ኪዳን 2023 (እ.አ.አ)
ታህሳስ 4–10 (እ.አ.አ)። ራዕይ 1–5፦ “ክብር … ኃይልም … ለበጉ ይሁን”


“ታህሳስ 4፟–10 (እ.አ.አ)። ራዕይ 1–5፦ ‘ክብር … ኃይልም … ለበጉ ይሁን’” ኑ፣ ተከተሉኝን—ለግለሰቦች እና ለቤተሰቦች፦ አዲስ ኪዳን 2023 (እ.አ.አ) (2022)

“ታህሳስ 4፟–10 (እ.አ.አ)። ራዕይ 1–5፣” ኑ፣ ተከተሉኝ—ለግለሰቦች እና ለቤተሰቦች፦ 2023 (እ.አ.አ)

ምስል
ጠቦት ሳር ላይ ተቀምጦ

ታህሳስ 4፟–10 (እ.አ.አ)።

ራዕይ 1–5

“ክብር … ኃይልም … ለበጉ ይሁን”

ራዕይውስጥ ስላነበባችሁት ያላችሁን ጥያቄዎች ለመፃፍ አስቡ። ከዚያ ለጥያቄዎቻችሁ መልስ መፈለግ ወይም ከቤተሰብ አባል ጋር ወይም በቤተክርስቲያን ክፍሎች ውስጥ መወያየት ትችላላችሁ።

ያሳደረባችሁን ስሜት መዝግቡ

በኃይለኛ መንፈሳዊ ተሞክሮ ወቅት የተሰማችሁን ለሌሎች ለመግለጽ ተቸግራችሁ ታውቃላችሁ? የዕለት ተዕለት ቋንቋ መንፈሳዊ ስሜቶችን እና ግንዛቤዎችን ለመግለጽ በቂ እንዳልሆነ ሊሰማ ይችላል። ምናልባትም ዮሐንስ አስደናቂ መገለጡን ለመግለጽ እንዲህ ዓይነቱን የበለፀገ ምሳሌ እና ምስል የተጠቀመው ለዚህ ሊሆን ይችላል። እሱ በአጭሩ ኢየሱስ ክርስቶስን አይቶ እንደነበር መግለፅ ይችል ነበር፣ ነገር ግን የእርሱን ተሞክሮ ለመረዳት እንድንችል አዳኙን “ዓይኖቹ እንደ እሳት ነበልባል፣” “ከአፉም በሁለት ወገን የተሳለ ስለታም ሰይፍ ወጣ፣” እና “ፊቱም በኃይል እንደሚበራ እንደ ፀሐይ” ነበር በማለት ገለጸ (ራዕይ 1፥14–16)። የዮሐንስ ራእይ፣ መጽሐፍን ስታነቡ፣ ከእያንዳንዱ ምልክት በስተጀርባ ያለውን ትርጉም ባትረዱም፣ ዮሐንስ እናንተ እንድትማሩ እና እንዲሰማችሁ የፈለጋቸውን መልእክቶች ለማወቅ ሞክሩ። የቤተክርስቲያኗን ጉባኤን ከሻማ መቅረዝ፣ ሰይጣንን ከዘንዶ፣ ኢየሱስ ክርስቶስን ከበግ ጋር ያወዳደረው ለምን ሊሆን ይችላል? በመጨረሻ፣ በጣም አስፈላጊ የሆነውን ጭብጥ ጨምሮ ዋና ዋናዎቹን ጭብጦች ለመረዳት በራዕይ ውስጥ እያንዳንዱን ምልክት መረዳት አይጠበቅባችሁም፤ ኢየሱስ ክርስቶስ እና ተከታዮቹ በሰዎች እና በሰይጣን መንግስታት ላይ ድል ያደርጋሉ።

ምስል
የግል ጥናት ምልክት

ለግል የቅዱሳት መጻህፍት ጥናት ሃሳቦች

የዮሐንስ ራዕይ የሚያስተምረው የሰማይ አባት ልጆቹን ለማዳን ያለውን ዕቅድ ነው።

ራዕይ መጽሐፍ ለመረዳት አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል፣ ነገር ግን ተስፋ አትቁረጡ። የዮሐንስ ቃል ሙከራችሁን እንድትቀጥሉ ሊያነሳሳችሁ ይችላል፤ “ዘመኑ ቀርቦአልና የሚያነበው፣ እናም የሚሰሙ እና የሚረዱ የትንቢቱን ቃል የሚሰሙትና በውስጡ የተጻፈውን የሚጠብቁት ብፁዓን ናቸው” (ጆሴፍ ስሚዝ ትርጉም ራዕይ 1፥3 [በመጽሃፍ ቅዱስ አባሪ ውስጥ]፣ አጽንኦት ተጨምሮበታል)።

ራዕይ ን ለማጥናት አንደኛው መንገድ ከድህነት ዕቅድ ጋር ያለውን ግንኙነቶች በመፈለግ ነው። ይህ አጠቃላይ እይታ ሊረዳችሁ ይችላል፦

  • ምዕራፍ 5 እና12 በቅድመ ሕይወት ውስጥ ያሉትን ክስተቶች ይገልጻሉ።

  • ምዕራፍ 6–1113–1416–19 ስለምድራዊ ህይወት እና በምድር ታሪክ ውስጥ ስለነበሩ ክስተቶችን ይገልፃል።

  • ምዕራፍ 2–31520–22 የመጨረሻውን ፍርድ እና ታማኞችን ስለሚጠብቀው ክብር ይገልፃል።

በምታነቡበት ጊዜ ራሳችሁን ጠይቁ፣ “ይህ ስለ እግዚአብሔር ዕቅድ ምን ያስተምረኛል? ክፉን አሸንፌ ወደ እርሱ እንድመለስ እግዚአብሔር ምን አደረገልኝ? ለታማኞች የገባው ቃል ምንድር ነው?

ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 77ራዕይ ውስጥ ያሉትን አንዳንድ ምልክቶች የሚያብራራ መሆኑን ማወቁ ጠቃሚ ሊሆን ይችላል። በተጨማሪም፣ የጆሴፍ ስሚዝ ትርጉም በራእይ፣ ውስጥ በርካታ ምንባቦችን ያብራራል፣ ስለዚህ የግርጌ ማስታወሻዎቹን እና የመጽሐፍ ቅዱስ መጨረሻ በመደበኛነት ፈትሹ።

በተጨማሪም የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ–ቃላትን “ዮሐንስ፣” የ“ዮሐንስ ራእይ” ን ተመልከቱ።

ራዕይ 1

ኢየሱስ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ሕያው ልጅ ነው።

ራዕይ የመጀመሪያ ምዕራፍ የኢየሱስ ክርስቶስ በራዕይ ለዮሐንስ መገለጥን ይገልጻል። ምናልባት ይህ ምዕራፍ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚናገረውን ሁሉ፣ እሱ ማን እንደ ሆነ፣ ለእኛ ምን እንደሚሠራ እና ምን እንደሚመስል ዝርዝር ማዘጋጀት ትችላላችሁ።

አንዳንድ የምትማሯቸው ነገሮች ከምልክቶች ይመጣሉ። በእነዚህ ምልክቶች ጌታ ስለራሱ ሊያስተምራችሁ የሚሞክረውን አስቡ። ለምሳሌ፣ አዳኙ ራሱን “መጀመሪያ እና መጨረሻ” እና “የመጀመሪያው እና የመጨረሻው” ብሎ እንደጠራ አስተውሉ። እነዚህ ማዕረጎች ለምን ጉልህ ናቸው ብላችሁ ታስባላችሁ? እነዚህ ማዕረጎች ስለ አዳኙ ምን ያስተምሯችኋል?

ራዕይ 2–3

ኢየሱስ ክርስቶስ በግል ያውቀኛል እናም ፈተናዎቼን እንድወጣ ይረዳኛል።

ራዕይ 2–3 ውስጥ የአዳኙ ቃላት በዮሐንስ ዘመን ስለነበሩ ስለ እያንዳንዱ የቤተክርስቲያኗ ቅርንጫፎች ስኬቶችን እና ትግሎችን እንደተረዳ ያሳያሉ። የቅዱሳኑን ጥረት አድንቋል፤ ለመለወጥ ስለሚያስፈልጋቸው ነገሮችም አስጠንቅቋል። ከአዳኙ ውዳሴ እና ማስጠንቀቂያዎች ምን ትማራላችሁ?

አዳኙ የእናንተን ስኬቶቻችሁን እና ትግሎቻችሁንም ይረዳል፣ እናም ሊረዳችሁ ይፈልጋል። እሱ ድል ለሚነሱ የሚሰጠውን ተደጋጋሚ ተስፋዎች ልብ ይበሉ። ስለ እነዚህ ተስፋዎች ምን ያስደንቃችኋል? ጌታ ምን እንድታሸንፉ ይፈልጋል? የእርሱን እርዳታ ለመቀበል ምን ማድረግ ትችላላችሁ?

ራዕይ 4–5

የሰማይ አባት ዕቅድን እውን ማድረግ የሚችለው ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው።

ራዕይ 4 ስለ ሰማይ አባት እና ከ ራዕይ 5፣ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ምን ትማራላችሁ? ኢየሱስ ክርስቶስ (“በጉ”) የሰማይ አባት ዕቅድን እንደሚፈጽም ሁላችንም ስንረዳ እንዴት እንደነበር አስቡ (አዳኙ “መጽሐፉን ይዘረጋ ዘንድ ሰባቱንም ማኅተም [መፍታት]”ራዕይ 5፥5ይችላል።) ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ለምን ይህንን ማድረግ ቻለ? እንደ አዳኛችሁ በእርሱ ላይ እምነታችሁን እንዴት ማሳየት ትችላላችሁ?

በተጨማሪም እዮብ 38፥4–7ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 77፥1–7፣ ተመልከቱ።

ምስል
የቤተሰብ ጥናት ምልክት

ለቤተሰብ ቅዱሳት መጻህፍት ጥናትና ለቤተሰብ የቤት ምሽት ሃሳቦች

ራዕይ1፥20ኢየሱስ ቤተክርስቲያኑን ከሻማ መቅረዞች ጋር ያወዳደረው ለምንድነው? (ማቴዎስ 5፥14–16ን ተመልከቱ)። በመቅረዝ ላይ እንደ ብርሃን መሆን እንደምንችል ስለሚናገር መዝሙር ዘምሩ፣ ለምሳሌ “አብራ” (የልጆች መዝሙር፣ 144)

ራዕይ 2–3ዮሐንስ በዘመኑ ለቤተክርስቲያናት እንደሰጣቸው መልእክት ለቤተሰባችሁ እንዲሰጥ እንደተጠየቀ አስመስሉ። እሱ ምን በጥሩ ሁኔታ እየሄደ ነው ሊል ይችላል? እንዴት ማሻሻል ትችላላችሁ?

ራዕይ 73፥15–16እነዚህን ጥቅሶች ካነበባችሁ በኋላ ቤተሰባችሁ ለብ ያለን ነገር የበለጠ ሙቅ ወይም ቀዝቃዛ የሆነን ነገር ሊጠጡ ይችላሉ። በመንፈሳዊነት ለብ ያለ መሆን ምን ማለት ነው?

ራዕይ 3፥20ቤተሰባችሁ ራዕይ 3፥20ን ሲያነብ አዳኙ በር የሚያንኳኳበትን ምስል አሳዩ (የዚህን ረቂቅ መጨረሻ ተመልከቱ)። ኢየሱስ ወደ ውስጥ ከመግባት ይልቅ ለምን ያንኳኳል? የቤተሰብ አባላት በየተራ በር ማንኳኳት ይችላሉ። ከዚያ በቤተሰብ ውስጥ ሌላ ሰው ለአዳኙ “[በሩን የምንከፍትበት]” መንገድ ሊጠቁም እና የቤተሰቡ አባል እንዲገባ ሊያደርግ ይችላል። አዳኙ በቤታችን ውስጥ ቢኖር ምን የሚሰማን ይመስላችኋል?

ራዕይ 4፥10–11የሰማይ አባትን ማምለክ ምን ማለት ነው? እርሱን እንድናመልክ የሚያደርገንን ስለ እርሱ ምን እናውቃለን?

ራዕይ 5፥6፣ 12–13ኢየሱስ ክርስቶስ “በግ” የተባለው ለምንድን ነው? ይህ ማዕረግ ስለ እርሱ ምን ያስተምረናል?

ልጆችን ለማስተማር ተጨማሪ ሃሳቦችን ለማግኘት የዚህን ሳምንት ዝርዝርኑ፣ ተከተሉኝ—ለመጀመሪያ ክፍል ተመልከቱ።

በሀሳብ የሚቀርብ መዝሙር፥ “ኢየሱስ፣” መዝሙር፣ቁጥር 196።

የምናስተምርበትን ዘዴ ማሻሻል

ጥያቄዎችን መጠየቅ አበረታቱ። ጥያቄዎች የቤተሰብ አባላት ለተማሩበት ምላሽ እንዴት እንደሚሰጡ ለመማር እና ግንዛቤ ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን የሚያመለክቱ ናቸው። በቅዱሳት መጻህፍት ውስጥ መልሶችን እንዴት ማግኘት እንደሚችሉ ቤተሰባችሁን አስተምሩ። (በአዳኙ መንገድ ማስተማር25–26ን ተመልከቱ።)

ምስል
ክርስቶስ በር እያንኳኳ

አስገቡት፣ በግሬግ ኬ. ኦልሰን

አትም