ብሉይ ኪዳን 2022 (እ.አ.አ)
ነሐሴ 8–14 (እ.አ.አ)። መዝሙረ ዳዊት 1–2፤ 8፤ 19–33፤ 40፤ 46፥ “እግዚአብሔር እረኛዬ ነው”


“ነሐሴ 8–14 (እ.አ.አ)። መዝሙረ ዳዊት 1–2፤ 8፤ 19–33፤ 40፤ 46፥ ‘እግዚአብሔር እረኛዬ ነው,’” ኑ፣ ተከተሉኝ—–ለግለሰቦች እና ለቤተሰቦች፦ ብሉይ ኪዳን 2022 (እ.አ.አ) [2021 (እ.አ.አ)]

“ነሐሴ 8–14 (እ.አ.አ)። መዝሙረ ዳዊት 1–2፤ 8፤ 19–33፤ 40፤ 46፣” ኑ፣ ተከተሉኝ—ለግለሰቦች እና ለቤተሰቦች፥ 2022 (እ.አ.አ)

ምስል
ኢየሱስ ከጠቦት ጋር ሲራመድ

እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፣ በዮንግሱንግ ኪም፣ havenlight.com

ነሐሴ 8–14 (እ.አ.አ)

መዝሙረ ዳዊት 1–2819–334046

“እግዚአብሔር እረኛዬ ነው”

በመዝሙራት ምርጫ ወይም በዚህ ረቂቅ ውስጥ በተዘረዘሩት መርሆዎች ብቻ የመገደብ ስሜት አይሰማችሁ። ወደ ጌታ ለመቅረብ እንዲሰማችሁ ወደሚረዷችሁ እውነቶች መንፈስ ቅዱስ ይምራችሁ።

ያሳደረባችሁን ስሜት መዝግቡ

መዝሙረ ዳዊትን ማን እንደጻፈ በእርግጠኝነት አናውቅም። ጥቂቶቹ ንጉሥ ዳዊት እንደጻፋቸው ይታመናሉ፣ ግን አብዛኞቹ ፀሐፊዎች ስማቸው አልተገለጠም። ሆኖም መዝሙሮችን ካነበብን በኋላ፣ ስማቸውን ባናውቅም እንኳ የመዝሙረኞችን ልብ እንደምናውቅ ሆኖ ይሰማን ይሆናል። እኛ የምናውቀው መዝሙሮች በእስራኤላውያን መካከል ትልቅ የአምልኮ ክፍል እንደነበሩ፣ እና አዳኝ ብዙ ጊዜ እንደጠቀሳቸው ነው። በመዝሙሮች ውስጥ፣ ወደ እግዚአብሔር የጥንት ሰዎች ነፍስ ውስጥ የሚያሳይ መስኮትን እናገኛለን። ስለ እግዚአብሔር ምን እንደተሰማቸው፣ ምን እንዳስጨነቃቸው እና እንዴት ሰላም እንዳገኙ እናያለን። ዛሬ አማኞች እንደመሆናችን፣ በመላው ዓለም፣ አሁንም እነዚህን ቃላት ለእግዚአብሔር አምልኮአችን እንጠቀማለን። የመዝሙረ ዳዊት ጸሐፊዎች ወደ እኛ ነፍስ ውስጥ የሚያሳይ መስኮት የነበራቸው ይመስላል እናም ስለ እግዚአብሔር ያለንን ስሜት፣ ስለምንጨነቅበት እና ሰላምን እንዴት እንደምናገኝ የሚገልጹበት መንገድ ያገኙ ይመስላል።

ስለ መዝሙረ ዳዊት አጭር ማብራሪያ ለማግኘት በመፅሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ውስጥ “መዝሙረ ዳዊት“ የሚለውን ተመልከቱ።

ምስል
የግል ጥናት ምልክት

ለግል የቅዱሳት መጻህፍት ጥናት ሃሳቦች

መዝሙረ ዳዊት 12326–2846

መዝሙር ጌታን እንድናምን ያስተምረናል።

ጸሐፊዎቹ ፍርሃትን፣ ሀዘንን ወይም ጭንቀትን ምን ያህል ጊዜ እንደሚገልጹ መዝሙርን ስታነቡ ልብ ትሉ ይሆናል። ለእምነት ሰዎችም እንኳ፣ እንዲህ ያሉት ስሜቶች የተለመዱ ናቸው። ነገር ግን መዝሙሮችን የሚያነቃቃ የሚያደርጋቸው ቢኖር የሚሰጡዋቸው መፍትሄዎች ናቸው፣ እንዲሁም በጌታ ላይ ሙሉ መታመንን ጨምሮ። እናንተ መዝሙረ ዳዊት 12326–2846ን ስታነቡ፣ እነዚህን የሚያነሳሱ መልእክቶች አስቡ። የሚከተሉትን አስተውሉ፣ እና ግኝታችሁን ጻፉ፥

  • ጌታን ለመታመን ግብዣ፤

  • ጌታን የሚገልጹ ቃላት፤

  • እርሱ የሚሰጣቸውን ሰላም፣ ጥንካሬ፣ እና ሌሎች በረከቶች የሚገልጹ ቃላት፤

  • እርሱን የሚያምኑትን የሚገልጹ ቃላት፤

መዝሙረ ዳዊት 222

መዝሙሮች አእምሯችንን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት እና አገልግሎት ይጠቁማሉ።

በርካታ መዝሙሮች ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ምድራዊ ሕይወት ያመለክታሉ። በአዲስ ኪዳን ዘመን የነበሩ ክርስቲያኖችም እነዚህን ግንኙነቶች ተመልክተዋል—ለምሳሌ፣ በመዝሙረ ዳዊት 2 ውስጥ ኢየሱስ በንጉሥ ሄሮድስ እና በጴንጤናዊው ጰላጦስ ፊት ለፍርድ እንደቀረበ መጠቀሱን ተገንዝበዋል (የሐዋርያት ሥራ 4፥24–30ን ተመልከቱ)። እነዚህን ለማንበብ አስቡ፦ መዝሙረ ዳዊት 2 እና 22፣ በተጨማሪ ማቴዎስ 27፥35–46ሉቃስ 23፥34–35፤ እና ዮሐነስ 19፥23–24። በእነዚህ መዝሙሮች ውስጥ ባሉ ቃላት እና በአዳኝ ሕይወት መካከል ግንኙነቶችን ፈልጉ እና በሚቀጥሉት ጥቂት ሳምንቶች ውስጥ መዝሙረ ዳዊትን ስታጠኑ ተመሳሳይ ግንኙነቶችን መፈለጋችሁን ቀጥሉ።

መዝሙሮችን በደንብ የሚያውቁ እና ከአዳኝ ሕይወት ጋር ግንኙነቶችን የተመለከቱ በኢየሱስ ዘመን እንደነበሩ አይሁዳዊ አድርጋችሁ እራሳችሁን አስቡ። ይህ እውቀት ለእናንተ ምን ያህል በረከት ሆኖ ነበር?

በተጨማሪም መዝሙረ ዳዊት 31፥534፥2041፥9ሉቃስ 24፥44ዕብራዊያን 2፥9–12ን ተመልከቱ።

መዝሙረ ዳዊት 81933

“የእግዚአብሔር ቸርነት ምድርን ሞላች።”

መዝሙረ ዳዊት 819፤ እና 33 ን ማንበብ የጌታን ብዙ ድንቅ ፍጥረቶች እንድታስቡ ሊያነሳሳችሁ ይችላል። ያን ስታደርጉ ለሃሳባችሁ እና ስሜቶቻችሁ ትኩረት ስጡ። እንዴት የጌታ ፍጥረቶች ለእናንተ “የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ”? (መዝሙረ ዳዊት 19፥1)።

መዝሙረ ዳዊት 19፥7–1129

የጌታ ቃል “ልብን ደስ የሚያሰኝ” ኃይለኛ ነው።

በመዝሙራት ውስጥ እንደ ምስክር፣ ሕጎች፣ ትእዛዝ፣ እና ፍርዶች ያሉ ቃላት የጌታን ቃል ሊያመለክቱ ይችላሉ። እናንተ መዝሙረ ዳዊት 19፥7–11ን ስታነቡ ያንን በአእምሮአችሁ ያዙ። እነዚህ ጥቅሶችለእናንተ ስለጌታ ቃል ምን ይጠቁማሉ? መዝሙረ ዳዊት 29 ስለ እርሱ ድምጽ ምን ያስተምራችኋል? በእናንተ ተሞክሮ፣ የጌታ ቃል ወይም ድምጽ ከእነዚህ መግለጫዎች ጋር እንዴት ነው የሚዛመደው?

ምስል
ኮንስፕሲኦን ቺሊ ቤተመቅደስ

ወደ ጌታ ፊት ለመግባት በመንፈሳዊ የጠራን እና ንጹህ መሆን አለብን።

መዝሙረ ዳዊት 2426–27

በጌታ ፊት መግባት ንጽህናን ይጠይቃል።

በኢየሩሳሌም ያለው ቤተመቅደስ የተገነባው በተራራ ላይ ስለሆነ “የእግዚአብሔር ተራራ” (መዝሙረ ዳዊት 24፥3) የሚለው ሐረግ ቤተ መቅደሱን ወይም የእግዚአብሔርን መኖር ሊያመለክት ይችላል። ያም እናንተ በመዝሙረ ዳዊት 24 ያላችሁ መረዳት ላይ ምን ይጨምራል? “እጆቹ የነጹ፣ ልቡም ንጹሕ” የሆነ ማለት ለእናንተ ምንድን ነው? (መዝሙር 24፥4)።

መዝሙረ ዳዊት 26 እና 27 ስለ ጌታ ቤት ምን ያስተምሯችኋል?

በተጨማሪም መዝሙረ ዳዊት 15፤ ዴቪድ ኤ. ቤድናር፣ “እጆቹ የነጹ እና ልቡም ንጹሕ፣” ሊያሆና፣ ግንቦት 2007 (እ.አ.አ)፣ 80–83 ተመልከቱ።

ምስል
የቤተሰብ ጥናት ምልክት

ለቤተሰብ ቅዱሳት መጻህፍት ጥናትና ለቤተሰብ የቤት ምሽት ሃሳቦች

መዝሙረ ዳዊት 22አንድ የቤተሰብ አባል ይህንን መዝሙር ሲያነብ፣ ሌሎች በማቴዎስ 27፥35–46 ውስጥ የሚገኝ ተመሳሳይነትን መፈለግ ይችላሉ። ከዚያም ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እና ለእኛ ስለከፈለው መስዋዕትነት ስሜቶቻቸውን ሊያካፍሉ ይችላሉ።

መዝሙረ ዳዊት 23መዝሙረ ዳዊት 23፣ እንደ “ጌታ እረኛዬ ነው” እና “ጌታ መስኬን ያዘጋጃል” (መዝሙሮች፣ ቁጥሮች 108፣ 109) ላሉ ለብዙ መዝሙሮች መነሳሻ ነበር። ምናልባት ቤተሰባችሁ ከእነዚህ መዝሙሮች ውስጥ አንዱን መዘመር እና በመዝሙሩ ውስጥ ግጥሞቹን ሊያነሳሱ የሚችሉ ቃላትን መለየት ይፈልጉ ይሆናል። ወይም በመዝሙሩ ውስጥ ያገኙትን አንድ ነገር ስዕሎችን በመሳል እና የቤተሰብ አባላት ከስዕሎቹ ጋር የሚሄዱትን ጥቅሶች ወይም ግጥሞች እንዲገምቱ በማድረግ ሊደሰቱ ይችላሉ። አዳኝ እንደ እረኛ የሆነልን እንዴት ነው?

መዝሙረ ዳዊት 24፥3–5ንፁህ እጆች እና ንፁህ ልብ መኖሩ አስፈላጊነት ላይ አፅንዖት ለመስጠት፣ የቤተሰብ አባላት እጃቸውን ሲታጠቡ መዝሙረ ዳዊት 24፥3–5ን ማንበብ ትችላላችሁ። በዚህ መዝሙር ውስጥ እጆች ምን ሊወክሉ ይችላሉ? ልብ ምንን ሊወክል ይችላል? እጃችንን እና ልባችንን በመንፈሳዊ ለማንጻት ምን ማድረግ አለብን?

መዝሙረ ዳዊት 30፥5፣ 11መዝሙረ ዳዊት 30፥5 “ልቅሶ ማታ ይመጣል፥ ጥዋት ግን ደስታ ይሆናል” የሚለውን ቃል ኪዳን ይዟል። ጌታ ሀዘናችንን ወደ ደስታ የቀየረው እንዴት ነው? ቁጥር 11 የሚያብራራውን ቤተሰባችሁ በጭውውት መልክ ማሳየት ይችላሉ።

መዝሙረ ዳዊት 33በዚህ መዝሙር ውስጥ ሁሉም ቃል ምን ያህል ጊዜ ጥቅም ላይ እንደዋለ አስተውሉ። በተለይ በቁጥሮች 13–15 ተደጋግሞ ከተጠቀሰው ከዚህ ቃል ስለጌታ ምን እንማራለን?

መዝሙረ ዳዊት 46፥10የቤተሰብ አባላት “እረፉ” እንደሚለው ለማድረግ በአንድነት አንድ ነገርን ልታደርጉ ትችላላችሁ። ማረፍ እግዚአብሔርን ማወቅ እንድንችል እንዴት ሊረዳን ይችላል? እንድናርፍ እና እግዚአብሔርን ወደማወቅ ለመምጣት ምን ዕድሎች አሉን?

ልጆችን ለማስተማር ተጨማሪ ሃሳቦችን ለማግኘት፣ የዚህን ሳምንት ዝርዝርኑ፣ ተከተሉኝ—ለመጀመሪያ ክፍል ውስጥ ይመልከቱ።

በሀሳብ የሚቀርብ መዝሙር፥ “እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፣” መዝሙር፣ ቁጥር 108።

የግል ጥናትን ማሻሻል

አዲስ ነገር ፈጣሪ ሁኑ። እንደ መዝሙረ ዳዊት ያሉ ቅዱሳት መጻህፍት ሰዎች ጌታን ለማሞገስ አዲስ ፈጠራ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ያነሳሳሉ። በሙዚቃ፣ ግጥም፣ በሚታይ ጥበብ፣ ወይም በሌላ መንገድ መሰጠታችሁን መግለጽ የምትፈልጉ ከሆነ፣ በእነዚያ ስሜቶች ላይ ተግብሩ። በሰማይ አባት እና በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ሌሎች እምነታቸውን እንዲገነቡ ለመርዳት የፈጠራችሁትን ለማካፈል አስቡ።

ምስል
ኢየሱስ በግ በትከሻው ተሸክሞ

መልካሙ እረኛ፣ በኬን ስፔንሰር

አትም