2022 (እ.አ.አ)
መጽሐፈ ሞርሞንን በየቀኑ የማንበብ በረከት
ሚያዝያ 2022 (እ.አ.አ)


የክልል አመራር መልእክት

መጽሐፈ ሞርሞንን በየቀኑ የማንበብ በረከት

በሕይወቴ ውስጥ እውነት ሆኖ ያገኘሁት ተዛማጅ ቃል ኪዳን አለ። ይህ ቃል ኪዳን በዕለት ተዕለት ሕይወታችን ውስጥ መገለጥን ከመቀበል ጋር የተያያዘ ነው።

በ2007 (እ.አ.አ) ዩናይትድ ስቴትስ በኢኮኖሚ ውድቀት መሃል ነበረች። በዚህ የኢኮኖሚ ማሽቆልቆል ምክንያት፣ አንዳንድ የንግድ ደንበኞቼ ለኪሳራ ማመልከቻ ያስገቡ እና ንግዶቻቸውን ይዘጉ ነበር። ይህ ንግዴን እየጎዳው ነበር። ቤተሰቤን ለመንከባከብ እና ደንበኞቼን ለመርዳት ስፈልግ፣ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ከሰማይ አባት መመሪያ እፈልግ ነበር። ግልጽ መልስ አላገኘሁም እና ምን ማድረግ እንዳለብኝ አላውቅም ነበር። አንድ ቀን ጠዋት ስጸልይ እና በዚህ ችግር ላይ ሳሰላስል፣ መፅሐፈ ሞርሞንን አንስቼ ማንበብ ጀመርኩ። ይህን ድንቅ መጽሐፍ ሳነብ ደንበኞቼን ለመርዳት እና ንግዴን ለመርዳት ምን ማድረግ እንደምችል ሀሳቦች ወደ አእምሮዬ ሲመጡ ተሰማኝ። ይህም ለጸሎቶቼ ግልጽ መልስ ነበር።

በመፅሐፈ ሞርሞን መግቢያ ላይ፣ ግብዣ እና ቃል ኪዳን አለ። የሁሉም የእግዚአብሔር ልጆች ግብዣም ይህን እንዲያነቡት እና እውነት መሆኑን ለማወቅ እንዲፈልጉ ነው። መፅሐፈ ሞርሞን እውነት እንደሆነ ከመንፈስ ቅዱስ መለኮታዊ ምስክር ለሚያገኙ ሰዎች የተገባው ቃልንም ኢየሱስ ክርስቶስ የአለም አዳኝ እንደሆነ፣ ጆሴፍ ስሚዝ የእሱ መገለጥ እና በእነዚህ የመጨረሻ ቀናት ውስጥ ነቢይ እንደሆነ፣ እና ለመሲሁ ዳግም ምጽአት ለመዘጋጀት የኋለኛው ቀን ቅዱሳን የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን እንደገና በምድር ላይ የተመሰረተች የጌታ መንግስት እንደሆነች በዚያው አይነት ሀይል ለማወቅ እንደሚችሉ ነው።

በህይወቴ ውስጥ እውነት ሆኖ ያገኘሁት ሌላ ተዛማጅ ቃል ኪዳን አለ። ይህም ቃል ኪዳን በዕለት ተዕለት ህይወታችን ውስጥ መገለጥን ከመቀበል ጋር የተያያዘ ነው።

መፅሐፈ ሞርሞንን በተመለከተ ነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ እንዲህ ብሏል፦ “ለወንድሞች መፅሐፈ ሞርሞን በምድር ካሉ መፅሐፍት በሙሉ የበለጠ ትክክል እንደሆነ፣ እናም የኃይማኖታችን የማዕዘን ድንጋይ እንደሆነ፣ እናም ከየትኛውም መፅሐፍ በበለጠ በውስጡ ባሉት አዕምሮአዊ ትእዛዝ በመኖር ሰው ወደ እግዚአብሔር ሊቀርብ ይችላል ብዬ ነገርኳቸው።” 1

መፅሐፈ ሞርሞንን በእውነተኛ ፍላጎት ስናነብ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ የአለም አዳኝ መሆኑን እና የኋለኛው ቀን ቅዱሳን የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የጌታ በምድር ላይ ዳግም የተመሰረተች መንግስት መሆኗን አረጋግጠን ብቻ ሳይሆን፣ ነገር ግን አሁን እያጋጠሙን ስላሉ ጥያቄዎች ወይም ተግዳሮቶች በህይወታችን ተጨማሪ መገለጦችን ልንቀበል እንችላለን።

የአምላክ ሦስተኛው አባል የሆነው መንፈስ ቅዱስ ብዙ ኃላፊነቶች አሉት። ከብዙ ኃላፊነቱ መካከል የእውነት መስካሪ፣ ገላጭ፣ አጽናኝ እና አስተማሪ መሆን ይገኙበታል።

ስለ መንፈስ ቅዱስ በመናገር፣ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳስተማረው፣ “ነገር ግን እርሱ የእውነት መንፈስ [መንፈስ ቅዱስን የሚያመለክት] በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል፤ የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል እንጂ ከራሱ አይነግርምና፤ የሚመጣውንም ይነግራችኋል” (ዮሀንስ 16፥13፣ ትኩረት ተጨምሯል)።

አዳኙ ስለ መንፈስ ቅዱስም ይህንን እውነት አስተማረ፦ “አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል” (ዮሐንስ 14፥26፣ ትኩረት ተጨምሯል)። በተጨማሪም መጽሐፈ ሞርሞን በሞሮኒ 10፥5 ላይ “በመንፈስ ቅዱስ ኃይል የሁሉንም ነገር እውነታ ታውቁታላችሁ።”

ብዙ ጊዜ እግዚአብሔር እንዲመራን እንጸልያለን። የቤተሰብ ጉዳዮችን፣ ወይም ግንኙነቶችን፣ ወይም ሥራን፣ ወይም እያጋጠሙን ያሉ የግል ችግሮችን ለመፍታት መመሪያን ልንጠይቅ እንችላለን። እግዚአብሔር ጸሎታችንን ከሚመልስባቸው መንገዶች አንዱ በመንፈስ ቅዱስ በኩል ነው።

በራሴ ህይወት፣ መፅሐፈ ሞርሞንን ሳነብ፣ መንፈስ ቅዱስ የማነበውን እውነት ሲመሰክር ዘወትር እንደሚሰማኝ ተረድቻለሁ። እና ከዚያ ተጨማሪ በረከቶችን እቀበላለሁ። መንፈስ ቅዱስ በመፅሐፈ ሞርሞን ውስጥ ስላሉት ቃላቶች እውነት እንደሚመሰክር ስለሚሰማኝ፣ እሱ እነዚህን እውነቶች እየመሰከረ ሳለ፣ ልቤ እና አእምሮዬ በሌሎች የህይወቴ ገጽታዎች ምን ማድረግ እንዳለብኝ ሌሎች ግንዛቤዎችን ለመቀበል ክፍት ናቸው። መንፈስ ቅዱስ በእርግጥም “በእውነት ይመራኛል” እና “ቅዱሳት መጻህፍት ቃል በገቡት መሰረት ሁሉንም ነገር ያስተምረኛል።” በሥራ ጉዳዮች እና በቤተሰብ ጉዳዮች ላይ መመሪያ አግኝቻለሁ። በቤተክርስቲያን ጥሪዎች መመሪያ ተቀብያለሁ እና ሌሎች እያጋጠሙኝ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት እገዛን አግኝቻለሁ።

መፅሐፈ ሞርሞንን ሳነብ፣ መንፈስ ቅዱስ የመልእክቱን እውነት እንዲመሰክር በር እንደከፈትኩ ነኝ። እርሱም የመልእክቱን እውነት ሲመሰክር፣ እኔ የምሰማ እና የምሻ ከሆንኩኝ፣ በሌሎች የህይወቴ ገጽታዎች ምን ማድረግ እንዳለብኝ ተጨማሪ መመሪያ አገኛለሁ።

በመፅሐፈ ሞርሞን፣ ይህንን እውነት እንማራለን፦ “እነሆም፣ በድጋሚ እላችኋለሁ በመንገዱ የምትገቡ፣ እናም መንፈስ ቅዱስን የምትቀበሉ ከሆነ፣ ማድረግ ያለባችሁን ነገሮች ሁሉ ያሳያችኋል” (2 ኔፊ 32፥5)።

መፅሐፈ ሞርሞንን እንድታነቡ እጋብዛችኋለሁ። በየቀኑ አንብቡት። የዚህን እውነት የሚያረጋግጥ ምስክር ከመንፈስ ቅዱስ ተቀበሉ። የኢየሱስ ክርስቶስን መለኮታዊ ተልእኮ እና የእግዚአብሔር መንግስት በምድር ላይ በዳግም ስለመቋቋሟ የማረጋገጫ ምስክርነት ዛሬ ተቀበሉ። እና ከዚያም መመሪያን እና ትምህርቶችን እና በሌሎች የህይወታችሁ ገጽታዎች ከመንፈስ ቅዱስ እርዳታ ለመቀበል ዝግጁ ሁኑ። የምትፈልጉት ከሆናችሁ ይህም ወደ እናንተ ሊመጣ እንደሚችል እመሰክራለሁ።

ማቲው ኤል. ካርፔንተር በመጋቢት 2018 (እ.አ.አ) እንደ አጠቃላይ ባለስልጣን ሰባ ተጠርተዋል። እርሳቸውም ሚሼል (ሼሊ) ኬይ ብራውንን አግብተዋል፤ እነርሱም የአምስት ልጆች ወላጆች ናቸው።

ማስታወሻዎች

  1. መግቢያ፦ መፅሐፈ ሞርሞን።

አትም