ብሉይ ኪዳን 2022 (እ.አ.አ)
በአእምሮ ሊያዝ የሚገቡ ሀሳቦች፥ “ኢየሱስ ለእስራኤል ሁሉ እንዲህ ይላል፣ ‘ወደቤት ኑ’”


“በአእምሮ ሊያዝ የሚገቡ ሀሳቦች፥ ‘ኢየሱስ ለእስራኤል ሁሉ እንዲህ ይላል፣ “ወደቤት ኑ፣”’” ኑ፣ ተከተሉኝ—ለግለሰቦች እና ለቤተሰቦች፥ ብሉይ ኪዳን 2022 (እ.አ.አ) [2021 (እ.አ.አ)]

“በአእምሮ ሊያዝ የሚገቡ ሀሳቦች፥ ‘ኢየሱስ ለእስራኤል ሁሉ እንዲህ ይላል፣ “ወደቤት ኑ”’” ኑ፥ ተከተሉኝ—ለግለሰቦች እና ለቤተሰቦች፥ ብሉይ ኪዳን 2022 (እ.አ.አ)

ምስል
የሀሳቦች ምልክት

በአእምሮ ሊያዝ የሚገቡ ሀሳቦች

“ኢየሱስ ለእስራኤል ሁሉ እንዲህ ይላል፣ ‘ወደቤት ኑ’”

በሲና ምድረበዳ ውስጥ ሙሴ የእስራኤልን ልጆች በተራራ ስር ሰበሰበ። እዚያ ጌታ በቅርቡ ነፃ የወጡ ባሪያዎችን ወደ ኃያል ህዝብ መለወጥ እንደሚፈልግ አወጀ። “የካህናት መንግሥት የተቀደሰም ሕዝብ ትሆኑልኛላችሁ” (ዘጸአት 19፥6) አላቸው። እጅግ በጣም ትልልቅ እና ጠንካራ በሆኑ ጠላቶች በሚከበቡበት ጊዜም እንኳን እነርሱ እንደሚለሙ እና እንደሚበለፅጉ ቃል ገባ (ዘዳግም 28፥1–14ን ይመልከቱ)።

ይህ ሁሉ የሚሆነው እስራኤላውያን ብዙ ወይም ጠንካራ ወይም ችሎታ ያላቸው በመሆናቸው አልነበረም። የሚሆነውም “ቃሌን በእውነት ብትሰሙ ኪዳኔንም ብትጠብቁ” (ዘጸአት 19፥5) ነው ብሎ ጌታ አብራራ። ታላቅ ያደረጋቸው የራሳቸው ሳይሆን፣ የእግዚአብሔር ሃይል ነበር።

ሆኖም እስራኤላውያን ሁል ጊዜ ድምፁን አልታዘዙም፣ እና ከጊዜ በኋላ ቃል ኪዳኑን መጠበቅ አቆሙ። ብዙዎች ሌሎች አማልክትን ማምለክ እና በአካባቢያቸው ያሉትን ባህላዊ ልምዶች መቀበል ጀመሩ። ከሌላው ሁሉ የሚለይ ህዝብ ያደረጋቸውን ነገር ማለትም ከጌታ ጋር የቃል ኪዳን ግንኙነታቸውን ውድቅ አደረጉ። የእግዚአብሔር ሃይል ሳይጠብቃቸው (2 ነገሥት 17፥6–7ን ይመልከቱ)፣ ጠላቶቻቸውን የሚያስቆም ምንም አልነበረም (2 ዜና 36፥12–20ን ይመልከቱ)።

መበታተን

ከ735 እስከ 720 ም.ዓ. ገደማ መካከል፣ አሶራውያን ከአሥራ ሁለቱ ነገዶች ወደ አሥሩ የሚገኘውን የሰሜኑን የእስራኤል መንግሥት በመውረር በሺዎች የሚቆጠሩ እስራኤላውያንን ወደ ተለያዩ የአሶር ግዛቶች ወሰዱ (2 ነገሥት 17፥1–7ን ይመልከቱ)።1 እነዚህ እስራኤላውያን ከትውልድ አገራቸው ስለተወገዱና ወደ ሌሎች ብሔራት በመበተናቸው በከፊል “የጠፉ ነገዶች” በመባል ይታወቃሉ። ነገር ግን እነርሱ በተጨማሪ በጥልቅ ስሜት ውስጥ ጠፍተዋል፥ ከጊዜ በኋላ እንደ እግዚአብሔር የቃል ኪዳን ሰዎች የመሆን ስሜታቸውን አጥተዋል።

የደቡባዊው የይሁዳ መንግሥት አንዳንድ ጊዜ ከሰሜን መንግሥት የበለጠ ጽድቅ ስለነበር፣ ረዘም ላለ ጊዜ ዘልቋል።2 ነገር ግን በመጨረሻ እዚያ ያሉት ሰዎችም እንዲሁ ከጌታ ፈቀቅ ብለዋል። አሶራውያን አብዛኞቹን የደቡብ መንግሥት አጠቁ እና ድል ነሱ፤ በተአምራዊ ሁኔታ የተጠበቀችው ኢየሩሳሌም ብቻ ነበረች (2 ነገሥት 19ኢሳያስ 10፥12–13ን ይመልከቱ)። በኋላም፣ በ597 እና 580 ም.ዓ. መካከል፣ ባቢሎናውያን ቤተመቅደሱን ጨምሮ ኢየሩሳሌምን አጥፍተው ብዙ የከተማዋን ነዋሪዎች ማረኩ (2 ነገሥት 24–252 ዜና 36ኤርሚያስ 3952ን ይመልከቱ)። ከ70 ዓመታት ገደማ በኋላ፣ የይሁዳ ቀሪዎች ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሰው ቤተመቅደሱን እንደገና እንዲገነቡ ተፈቅዶላቸው ነበር። ቢሆንም፣ አብዛኞቹ በባቢሎን ቆዩ።3

ትውልዶች እያለፉ ሲመጡ፣ ከሁሉም ነገዶች የመጡ እስራኤላዊያንን “ወደማያውቁአቸውም አሕዛብ ሁሉ በዐውሎ ነፋስ [ተበትነው” ነበር (ዘካሪያስ 7፥14፤ በተጨማሪም አሞጽ 9፥8–9ን ይመልከቱ)። አንዳንዶቹ በጌታ ወደ ሌሎች አገሮች ተወስደዋል (2 ኔፊ 1፥1–5ኦምኒ 1፥15–16)። እስራትን ለማምለጥ ( 2 ነገሥት 25፥22–26ኤርምያስ 42፥13–1943፥1–7ን ይመልከቱ) ወይም ለፖለቲካ ወይም ኢኮኖሚ ምክንያቶች ሌሎቹ እስራኤልን ትተው ሄደዋል።4

እነዚህን ክስተቶች የእስራኤል መበታተን እንለዋለን። እና ለበርካታ ምክንያቶች ስለ መበታተን ማወቅ አስፈላጊ ነው። አንደኛ ነገር፣ ያም የብሉይ ኪዳን ዋና ርዕስ ነው፥ ብዙ የብሉይ ኪዳን ነቢያት እስራኤልን ወደ መበታተን ያመጣውን የመንፈሳዊ ቁልቁል መውረድ ምስክሮች ነበሩ። ያንን መበታተን ቀድመው ያዩ እና ስለዚህ ያስጠነቀቁ ሲሆን አንዳንዶቹም በዚያም ዘመን ውስጥ ኖረዋል።5 በብሉይ ኪዳን ውስጥ የኢሳይያስን፣ የኤርምያስን፣ የአሞጽን እና የሌሎችንም ብዙ የመጨረሻ ክፍል መጻሕፍትን ስታነቡ ይህንን ማስታወሱ ጠቃሚ ነው። ይህ በአእምሮአችሁ እንዳለ፣ ስለ አሦር እና ባቢሎን፣ ስለ ጣዖት አምልኮ እና ስለ ምርኮ፣ ስለ ጥፋት እና በመጨረሻም ስለ ዳግም መመለስ ያላቸውን ትንቢት ስታነቡ ምን እየተናገሩ እንደሆነ ታውቃላችሁ።

የእስራኤልን መበታተንን መረዳቱ መፅሐፈ ሞርሞንንም በደንብ ለመረዳት ይረዳችኋል፣ ምክንያቱም መፅሐፈ ሞርሞን የተበታተነ የእስራኤል ቅርንጫፍ መዝገብ ክፍል ነው (1 ኔፊ 15፥12ን ይመልከቱ)። ይህ መዝገብ የሚጀምረው የሌሂ ቤተሰቦች ባቢሎናውያን ከማጥቃታቸው ጥቂት ቀደም ብሎ ወደ 600 ም.ዓ. አካባቢ ከኢየሩሳሌምን በሸሹት ነው። ስለ እስራኤል መበተን ትንቢት ከተናገሩ ነቢያት መካከል ሌሂ አንዱ ነበር።6 እናም ቤተሰቦቹ፣ የእስራኤልን ቤት ቅርንጫፍ አካል በመውሰድ በአለም ሌላኛው ክፍል፣ በአሜሪካ ውስጥ በመትከል፣ ያንን ትንቢት እንዲፈፀም አግዘዋል።

ምስል
ሰዎች የሚቃጠለውን ከተማ ትተው ሲሄዱ

የኢየሩሳሌም በናቡዘረዳን መደምሰስ፣ በዊልያም ብራሴይ ሆል © Providence Collection/licensed from goodsalt.com

መሰባሰብ

የእስራኤል መበታተን ግን የታሪኩ ግማሽ ብቻ ነው። ጌታ ህዝቡን አይረሳም፣ ቢተዉትም እንኳ ሙሉ በሙሉ አይተዋቸውም። እስራኤል እንደምትበታተን የነበሩት ብዙ ትንቢቶች አንድ ቀን እንደሚሰበሰቡ ቃል ኪዳን ከሚሰጥ ጋር ተያይዞ ነበር።7

ያም ቀን ዛሬ ነው—የእኛ ቀን። መሰባሰቡ ተጀምሯል። በ1836 (እ.አ.አ)፣ ሙሴ የእስራኤልን ልጆች በሲና ተራራ ስር ከሰበሰበ በኋላ በሺዎች ከሚቆጠሩ ዓመታት በኋላ፣ ሙሴ በከርትላንድ ቤተመቅደስ ውስጥ ለጆሴፍ ስሚዝ “ከምድር አራት ማዕዘናትን የእስራኤልን መሰብሰቢያ ቁልፎችን” ለመስጠት ተገለጸ (ትምህርት እና ቃልኪዳኖች 110፥11)። አሁን እነዚህን ቁልፎች በሚይዙ ሰዎች መሪነት፣ የጌታ አገልጋዮች መሄድ ከሚችሉበት፣ የእስራኤል ነገዶች ከእያንዳንዱ ህዝብ እየተሰበሰቡ ናቸው።

ፕሬዘዳንት ራስል ኤም. ኔልሰን ይህንን መሰብሰብ “ዛሬ በምድር ላይ እየተከናወነ ያለው እጅግ አስፈላጊ ነገር” ነው ብለውታል። ምንም ነገር በትልቅነት አይወዳደርም፣ ምንም ነገር በአስፈላጊነቱ አይወዳደርም፣ ምንም ነገር በግርማዊነት አይወዳደረውም። ምርጫችሁ ከሆነ፣ የምትፈልጉ ከሆነ፣ የዚያ ታላቅ ክፍል መሆን ትችላላችሁ።”8

እንዴት ነው ይህን የምታደርጉት? እስራኤልን መሰብሰብ ማለት ምን ማለት ነው? አሥራ ሁለቱን ነገዶች በአንድ ወቅት ወደ ነበሩበት ምድር መመለስ ማለት ነውን? በእርግጥም፣ ከዚያ እጅግ የላቀ፣ እጅግ በጣም ዘለአለማዊ የሆነ ማለት ነው። ፕሬዘዳንት ኔልሰን እንዳብራሩት፤

“ስለ መሰብሰብ፣ ስናወራ እያልን ያለነው ይህን ቀላል እውነታ ነው፤ እያንዳንዱ የሰማይ አባት ልጆች፣ በሁለቱም ማጋረጃ ጀርባ ያሉት፣ የኢየሱስ ክርስቶስን የተመለሰው ወንጌል መልእክትን መስማት ይገባቸዋል።

“በመጋረጃው በሁለቱም በኩል ማንንም ከእግዚአብሄር ጋር ቃልኪዳን ለመግባት እና አስፈላጊ የጥምቀት እና የቤተመቅደስ ስርዓቶችን ለመቀበል የሚረዳ ማንኛውንም ነገር በምታደርጉበት ጊዜ ሁሉ እስራኤልን ለመሰብሰብ እየረዳችሁ ነው። እንደዚያ ቀላል ነው።”9

ይህ የሚሆነው፣ ኢሳይያስ እንዳለው፣ “አንድ በአንድ” (ኢሳይያስ 27፥12) ወይም ኤርሚያስ አስቀድሞ እንዳለው፣ “ከአንዲት ከተማ ሁለቱንም ከአንድ ወገን” ነው (ኤርምያስ 3፥14)።

እስራኤልን መሰብሰብ ማለት የእግዚአብሔርን ልጆች ወደ እርሱ መመለስ ማለት ነው። እነርሱን ከእርሱ ጋር ወደ የቃል ኪዳኑ ግንኙነታቸው መመለስ ማለት ነው። ከረጅም ጊዜ በፊት ለማቋቋም ያቀደውን “ቅዱስ ሕዝብ” እንደገና ማቋቋም ማለት ነው (ዘጸአት 19፥6)።

ወደቤት ኑ

እንደ ቃል ኪዳን ጠባቂ፣ እናንተ የእስራኤል ቤት ክፍል ናችሁ።10 ተሰብስባችኋል፣ እና ሰብሳቢም ናችሁ። በእግዚአብሔር እና በአብርሃም ቃል ኪዳን የተጀመረው የዘመናት ድንቅ ታሪክ እስከ መጨረሻው እየተገነባ ነው፣ እናም እናንተ ቁልፍ ተዋናይ ናችሁ። “ኢየሱስ ለእስራኤል ሁሉ እንዲህ ይላል፣ ‘ወደቤት ኑ’”፣ ያም ጊዜ አሁን ነው።11

የሰብሳቢዎች መልእክት ይህ ነው፥ ወደ ቤታችሁ ወደ ኪዳኑ ኑ። ወደቤት ወደ ፅዮን ኑ። የእስራኤል ቅዱስ ወደሆነው ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ቤት ኑ፣ እና እርሱም ወደ አባታችሁ ወደ እግዚአብሔር ያመጣችኋል።

ማስታወሻዎች

  1. አስሩ በእስር የተማረኩት ነገዶች ሮቤል፣ ስምዖን፣ ይሳኮር፣ ዛብሎን፣ ዳን፣ ንፍታሌም፣ ጋድ፣ አሴር፣ ኤፍሬም እና ምናሴ ነበሩ። የክህነት ሃላፊነታቸውን ለመወጣት የሌዊ ነገድ አባላት በሌሎቹ ነገዶች ግዛት ውስጥ ተሰራጭተዋል።

  2. የደቡብ መንግሥት በዋናነት የይሁዳን እና የቢንያምን ጎሳ ያቀፈ ነበር። ሆኖም የበርካታ ሌሎች ነገዶች አባላት እዚያም ይኖሩ ነበር (2 ዜና 11፥14–17ን ይመልከቱ)። ለምሳሌ በኢየሩሳሌም ይኖር የነበረው ሌሂ ከምናሴ ነገድ ነበር።

  3. ዕዝራ 17ነህምያ 2ን ይመልከቱ። የባቢሎን ግዛት በፋርሳዊ መንግሥት ቁጥጥር ስር ዋለ። በርካታ የግዞት አይሁድ ቡድኖች ወደ ኢየሩሳሌም እንዲመለሱ የፈቀደው የፋርሳዊ ንጉሥ ቂሮስ ነበር።

  4. በ70 ዓ.ም. ኢየሩሳሌምና ቤተመቅደሷ እንደገና በሮሜ ተደምስሰው የቀሩ አይሁዶች በብዙ የምድር ብሔራት ተበተኑ።

  5. ኤርሚያስ 29፥18ሕዝቅኤል 22፥15ሆሴዕ 9፥17አሞጽ 9፥91 ኔፊ 1፥13

  6. በተጨማሪም 1 ኔፊ 1፥13–2010፥12–14ን ይመልከቱ።

  7. ኢሳይያስ 5፥2627፥1254ኤርምያስ 16፥14–1529፥1431፥10ሕዝቅኤል 11፥1734፥1237፥21–28ዘካርያስ 10፥81 ኔፊ 10፥1422፥253 ኔፊ 16፥1–517፥4ን ይመልከቱ።

  8. ራስል ኤም. ኔልሰን እና ዌንዲ ደብሊው. ኔልሰን፣ “የእስራኤል ተስፋ” [አለም አቀፍ የወጣቶች ጉባኤ፣ ሰኔ 3፣ 2018 (እ.አ.አ)]፣ ለNew Era እና ኤንዛይን፣ 8 ተጨማሪ፣ ChurchofJesusChrist.org

  9. ራስል ኤም. ኔልሰን እና ዌንዲ ደብሊው. ኔልሰን፣ “የእስራኤል ተስፋ፣” 15፣ ChurchofJesusChrist.org

  10. 2 ኔፊ 30፥2ን ይመልከቱ።

  11. አሁን እንደሰት፣” መዝሙር፣ ቁጥር 3።

አትም