2022 (እ.አ.አ)
አገልግሎት
ሰኔ 2022 (እ.አ.አ)


ከመመሪያ መጽሐፍ የተመረጡ

አገልግሎት

እኔና አናንተ አገልጋይ ወንድሞችና እህቶች መሆናችን እንዴት ያለ ታላቅ መብት ነው! The General Handbook [አጠቃላይ መመሪያ መጽሐፍ]፣ ክፍል 21፣ በአገልግሎት የክርስቶስን ምሳሌ እንድንከተል የሚረዱን አንዳንድ በመንፈስ የተነሳሱ ምክሮች ይሰጠናል።

አገልግሎት ማለት አዳኝ እንዳደረገው ሌሎችን ማገልገል ማለት ነው። በዙሪያው ያሉትን ወድዷል፣ አስተምሯል፣ ጸልዮላቸዋል፣ አፅናንቷል እንዲሁም ባርኳል።

ጌታ ሁሉም የቤተክርስቲያኑ አባላት እንደዚህ አይነት እንክብካቤ እንዲያገኙ ይፈልጋል።

ማገልገል እግዚአብሔርን እንድንወድ እና ጎረቤቶቻችንን እንድንወድ የተሰጠውን ትእዛዛት እንድንጠብቅ ይረዳናል። እንዲሁም የመዳን እና ከፍ ከፍ የማድረግ ስራን ለማከናወን የሚረዳ ወሳኝ መንገድ ነው።

የሽማግሌዎች ሸንጎዎች እና የሴቶች መረዳጃ ማህበር አመራሮች ሌሎችን እንዴት ማገልገል እንደምንችል እንድንማር ይረዱናል እናም መነሳሻን፣ መመሪያን እና ድጋፍን ይሰጡናል። እነርሱ እና እኛ ከቅዱሳት መጻህፍት፣ ከዚህ መመሪያው መፅሐፍ ምዕራፍ (21) በውስጥ፣ እና www.ministering.ChurchofJesusChrist.org ከሚለው ድህረ ገጽ መነሳሻን መፈለግ እንችላለን።

እኛ ጌታን እንወክላለን። አባላት የኤጲስ ቆጶሱን እና የሴቶች መረዳጃ ማህበር ወይም የሸንጎዎች መሪዎችን ፍቅር እና ድጋፍ እንዲሰማቸው እንረዳቸዋለን። አባላትን እንጠብቃለን እና ከእነርሱ ጋር አንድ ነን። በሰማይ አባት እና በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ያላቸውን እምነት ለማጠናከር እናግዛለን። ቅዱሳት ቃል ኪዳኖችን እንዲጠብቁ፣ ፍላጎቶቻቸውን እንዲለዩ፣ እነርሱን ለመርዳት እና ለማጽናናት እና በመንፈሳዊ እና በስጋዊ በራስ እንዲተማመኑ ለመርዳት እንረዳቸዋለን። ጥረታችንን ከወንድሞቻችንና ከእህቶቻችን ፍላጎት ጋር እናስተካክላለን።

አዳኙ ለደቀ መዛሙርቱ ትርጉም ያለው ሥራ ሰጣቸው። በተመሳሳይ መልኩ፣ እርሱ እንዳደረገው ለማገልገል ትርጉም ያለው ተልእኮ ተሰጥቶናል። የክርስቶስን ምሳሌ እንከተል፣ እናም ይህን በማድረግ፣ እኛ እና ወንድሞቻችንና እህቶቻችን የአዳኙ ፍቅር ይሰማናል።

አትም