አዲስ ኪዳን 2023 (እ.አ.አ)
ሐምሌ 31–ነሐሴ 6 (እ.አ.አ)። የሐዋሪያት ስራ 22–28፦ “አገልጋይና ምስክር”


“ሐምሌ 31–ነሐሴ 6 (እ.አ.አ)። የሐዋሪያት ስራ 22–28፦ ‘አገልጋይና ምስክር’” ኑ፣ ተከተሉኝን—ለግለሰቦች እና ለቤተሰቦች፦ አዲስ ኪዳን 2023 (እ.አ.አ) [2022 (እ.አ.አ)

“ሐምሌ 31–ነሐሴ 6 (እ.አ.አ)። የሐዋሪያት ስራ 22–28፣ “አገልጋይና ምስክር” ኑ፣ ተከተሉኝ—ለግለሰቦች እና ለቤተሰቦች፦ 2023 (እ.አ.አ)

ምስል
ጳውሎስ በእስር ቤት ውስጥ

ሐምሌ 31–ነሐሴ 6 (እ.አ.አ)

የሐዋሪያት ስራ 22-28

“አገልጋይና ምስክር”

ከመንፈስ ቅዱስ የሚመጡ ስሜቶች ብዙውን ጊዜ ጸጥ ያሉ እና ብልጭ የሚሉ ናቸው። ግንዛቤዎቻችሁን መመዝገብ በጥልቀት እንድታስቡባቸው ያስችላችኋል። የሐዋሪያት ስራ 22–28ን በምታነቡበት ጊዜ ወደ እናንተ የሚመጡትን ሀሳቦች እና ስሜቶች ጻፉ፤ እናም ለማሰላሰል ጊዜ ውሰዱ።

ያሳደረባችሁን ስሜት መዝግቡ

ፕሬዘደንት ቶማስ ኤስ ሞንሰን “እኛ በጌታ ተልእኮ ላይ ስንሆን፣ የጌታን እርዳታ የማግኘት መብት አለን” በማለት ቃል ገብተዋል (“ለመማር፣ ለማድረግ፣ ለመሆን፣” ሊያሆና፣ ህዳር 2008 (እ.አ.አ) 62)። ሆኖም ግን ለጥ ላለ መንገድ እና ማለቂያ ለሌለው የስኬት ፍሰት እኛ መብት የለንም። ለዚህ ማስረጃ፣ ከሐዋርያው ጳውሎስ የበለጠ ሌላን መመልከት አይገባንም። ከአዳኙ ተልእኮው “በአሕዛብም በነገሥታትም በእስራኤልም ልጆች ፊት [ስሙን] ይሸከም ዘንድ” ነበር (የሐዋሪያት ስራ 9፥15)። በየሐዋሪያት ስራ 22–28፣ ላይ ጳውሎስ ይህንን ተልዕኮ ሲፈጽም እና ከፍተኛ ተቃውሞ—ሰንሰለቶች፣ እስራት፣ አካላዊ ጥቃት፣ የመርከብ መሰበር እና የእባብ ጥቃት እንኳን ሲገጥመው እናያለን። ነገር ግን ኢየሱስ “በአጠገቡ ቆሞ፣ ጳውሎስ ሆይ፣ አይዞህ” ሲለው ” (የሐዋሪያት ስራ 23፥11) ደግሞ እኛ እናያለን። “በደስታ ድምፅ [ወንጌሉን ማወጅ]” “እኔ በመካከላችሁ ስላለሁ … ልባችሁን አንሱ እናም ተደሰቱ” ከሚል ቃል ኪዳን ጋር እንደሚመጣ የጳውሎስ ልምዶች የሚያነቃቁ ማሳሰቢያዎች ናቸው (ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 29፥4–5፤ በተጨማሪም ማቴዎስ 28፥19–20ን ተመልከቱ)።

ምስል
የግል ጥናት ምልክት

ለግል የቅዱሳት መጻህፍት ጥናት ሃሳቦች

የሐዋሪያት ስራ 22፥1–2126፥1–29

የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርት ምስክርነታቸውን በድፍረት ያካፍላሉ።

ጳውሎስ የሐዋሪያት ስራ 22 እና 26፣ ላይ የተመዘገቡትን ኃይለኛ ምስክርነቶች ሲያቀርብ በሮማ ወታደሮች እስረኛ ሆኖ ነበር። ያነጋገራቸው ሰዎች የሞት ፍርድ የመፍረድ ኃይል ነበራቸው። ሆኖም እሱ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እና እሱ ስለተቀበለው፥ “ከሰማይ [ስላየው] ራእይ” (የሐዋሪያት ስራ 26:19) በድፍረት ለመመስከር መረጠ። ስለእሱ ቃላት ምን ያነሳሳችኋል? ምስክርነታችሁን ለማካፈል ያላችሁን አጋጣሚዎች አስቡ። ለምሳሌ፣ ጓደኞቻችሁ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ምን እንዲሚሰማችሁ ያውቃሉ? ወይም የወንጌልን ምስክርነት እንዴት እንዳገኛችሁ ለመጨረሻ ጊዜ ለቤተሰቦቻችሁ ያካፈላችሁን መቼ ነው?

ወጣቱ ጆሴፍ ስሚዝ የመጀመርያ ራእዩን በመናገሩ ምክንያት ሲሳለቁበት ጳውሎስ ስለ ራእዩ በሰጠው ምስክርነት ተነሳስቶ ነበር (ጆሴፍ ስሚዝ—ታሪክ 1፥24–25ን ይመልከቱ)። ጆሴፍ ስሚዝ ከጳውሎስ የተማረውን እንዴት ታጠቃልላላችሁ? ስለ እነዚህ ሁለት የኢየሱስ ክርስቶስ ምስክሮች ምን ትማራላችሁ?

በተጨማሪም ኒል ኤል. አንደርሰን፣ “ስለ ክርስቶስ እናወራለን፣” ሊያሆና፣ ህዳር 2020 (እ.ኤ.አ) 88–91ን ተመልከቱ።

የሐዋሪያት ስራ 23፥10–1127፥13–25፣ 40–44

ጌታ እርሱን ለማገልገል ከሚጥሩት ጎን ይቆማል።

የጳውሎስ አገልግሎት በግልጽ እንደሚያሳየው በሕይወታችን ውስጥ ያሉ ችግሮች እግዚአብሔር እኛን ወይም የምንሠራውን ሥራ እንደማይቀበል የሚያሳይ ምልክት አይደለም። እንዲያውም፣ አንዳንድ ጊዜ በችግሮች ወቅት ነው የእርሱ ድጋፍ በሃይል የሚሰማን። ስለ ጳውሎስ አገልግሎት በቅርቡ ያነበባችሁትን መገምገም እና እሱ የጸናባቸውን አንዳንድ ነገሮች መዘርዘር አስደሳች ሊሆን ይችላል (ለምሳሌ የሐዋሪያት ስራ 14፥19–2016፥19–2721፥31–3423፥10–1127፥13–25፣ 40–44ን ተመልከቱ)። ጌታ ከጎኑ እንዴት ቆመ? እርሱ ከጎናችሁ እንዴት ቆመ?

የሐዋሪያት ስራ 24፥24–2726፥1–3፣ 24–29፣ 27

የእግዚአብሔር አገልጋዮች ቃላትን በመጠበቅ ደህንነት እና ሰላም አለ።

ጳውሎስ በአገልግሎቱ ሙሉ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እና ስለወንጌሉ ጠንካራ ምስክርነት ሰጥቷል። ብዙ ሰዎች ምስክርነቱን ተቀበሉ፣ ነገር ግን ሁሉም አይደሉም። የሐዋሪያት ስራ 24፥24–27 እና የሐዋሪያት ስራ 26፥1–3፣ 24–29ን በምታነቡበት ጊዜ የሚከተሉት በይሁዳ ያሉት የሮማውያን ገዥዎች ለጳውሎስ ትምህርቶች ምን ምላሽ እንደሰጡ የሚያሳዩ ቃላትን እና ሀረጎችን ፈልጉ።

  • ፊሊክስ

  • ፊስጦስ

  • ንጉሥ አግሪጳ

ጳውሎስ በቄሳር ለመፈተን ወደ ሮም ሲጓዝ በመርከቧ እና ተሳፋሪዎቿ ላይ “[ጥፋትና ብዙ ጕዳት እንዲሆን]” ተንብዮ ነበር (የሐዋሪያት ስራ 27፥10)። የጳውሎስ የመርከብ ባልደረቦች ለእሱ ማስጠንቀቂያዎች ምን ምላሽ እንደሰጡ ለማወቅ ምዕራፍ 27 ን አንብቡ። በእነሱ ተሞክሮ ውስጥ ለራሳችሁ ማንኛውንም ትምህርት ታገኛላችሁ?

የቤተክርስቲያኗን መሪዎች ትምህርት ስታደምጡ እንደእነዚህ ሰዎች ምላሽ ሰጥታችሁ ታውቃላችሁ? በእነዚህ መንገዶች ምላሽ መስጠት አንዳንድ የሚያስከትሉት ውጤቶች ምንድናቸው? የጌታን ምክር በአገልጋዮቹ ስለመቀበል ከእነዚህ ዘገባዎች ምን ትማራላችሁ?

በተጨማሪም 2 ኔፊ 33፥1–2፤ ዲ. ቶድ ክርስቶፈርሰን፣ “የማስጠንቀቅያ ድምፅ፣” ሊያሆና፣ ግንቦት 2017 (እ.አ.አ)፣ 108–11፤ “በህይወት ያለን ነቢይ ተከተሉ፣” የቤተክርስትያኗ ፕሬዝዳንቶች አስተምሮቶች፤ ኤዝራ ታፍት ቤንሰን (2014 (እ.አ.አ))፣ 147–55 ተመልከቱ።

ምስል
የቤተሰብ ጥናት ምልክት

ለቤተሰብ ቅዱሳት መጻህፍት ጥናትና ለቤተሰብ የቤት ምሽት ሃሳቦች

የሐዋሪያት ስራ 24፥16ጳውሎስ ከመቀየሩ በፊት በእግዚአብሔር ፊት ለረጅም ጊዜ የበደል ታሪክ ነበረው። ነገር ግን ንስሃ ለመግባት ፈቃደኛ ስለነበረ፣ “በእግዚአብሔር እና በሰው ላይ ሁል ጊዜ ንጹህ ሕሊና እንዲኖረኝ ራሴን አለማምዳለሁ” ለማለት ችሏል (ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 135፥4–5ን ተመልከቱ)። በእግዚአብሔር እና በሌሎች ላይ ከሚፈጸሙ ጥፋቶች ሕሊናችንን ነጻ ማድረግ እንዴት እንችላለን?

የሐዋሪያት ስራ 26፥16–18በእነዚህ ጥቅሶች ውስጥ ጌታ ጳውሎስን ምን እንዲያደርግ ጠራው? ተመሳሳይ ነገሮችን ለማድረግ ምን እድሎች አሉን?

የሐዋሪያት ስራ 28፥1–9በቤተሰባችሁ ውስጥ እባብ የሚወድ አለ? የሐዋሪያት ስራ 28:1–9፣ ላይ የተጠቀሱትን ታሪኮች ያንን ሰው ወይም ሌላ የቤተሰብ አባል እንዲናገር ልትፈልጉ ትችላላችሁ። ልጆቻችሁ የእነዚህን ታሪኮች ስዕል መሳል ወይም እነሱን በመተወን ሊደሰቱ ይችላሉ። ከእነዚህ ዘገባዎች ምን ትምህርት እናገኛለን? አንዱ ጌታ ለባሪያዎቹ የገባውን ቃል እንደሚፈጽም ነው። ለምሳሌ ማርቆስ 16፥18 ላይ የተሰጡትን ተስፋዎች በጳውሎስ ልምዶች ውስጥ ከተፈጸሙት ጋር ማወዳደር ትችላላችሁ። እንዲሁም ከቅርብ ጠቅላላ ጉባኤ ውስጥ ከጌታ አገልጋዮች በአንዱ—ምናልባትም ለቤተሰባችሁ ጠቃሚ የሆነ አንድ ቃል የተገባለትን ቃል ማግኘት እና በቤታችሁ ውስጥ ማሳየት ትችላላችሁ። ይህ ተስፋ እንደሚፈጸም እምነታችንን እንዴት ማሳየት እንችላለን?

ምስል
መርዛማ እባብ

ጳውሎስ መርዛማ እባብ ሲነድፈው እግዚአብሔር ጠብቆታል።

የሐዋሪያት ስራ 28፥22–24በጳውሎስ ዘመን እንደነበረው ቤተክርስቲያን (በቁጥር 22፣ ላይ “ወገን” ተብሎ የሚጠራው) ዛሬ ቤተክርስቲያን ብዙውን ጊዜ “[ተቃውሞ]” ይገጥማታል። ሰዎች አዳኙን እና ቤተክርስቲያኑን ሲቃወሙ ጳውሎስ ምን ምላሽ ሰጠ? ከጳውሎስ ተሞክሮ ምን እንማራለን?

ልጆችን ለማስተማር ተጨማሪ ሃሳቦችን ለማግኘት የዚህን ሳምንት ዝርዝርኑ፣ ተከተሉኝ—ለመጀመሪያ ክፍል ተመልከቱ።

በሀሳብ የሚቀርብ መዝሙር፦ “አዳኜ እንዳለ አውቃለሁ፣” መዝሙሮች፣ ቁጥር 135።

የምናስተምርበትን ዘዴ ማሻሻል

ቤተሰባችሁን በሚባርኩ መርሆዎች ላይ አተኩሩ። የእግዚአብሔርን ቃላት ስታጠኑ፣ ራሳችሁን እንዲህ ብላችሁ ጠይቁ፣ “ለቤተሰቤ የተለየ ትርጉም የሚኖረውን በዚህ የማገኘው ምንድን ነው?” (Teaching in the Savior’s Way [በአዳኙ መንገድ ማስተማር]፣ 17ን ይመልከቱ።)

ምስል
ጳውሎስ በንጉሥ አግሪጳ ፊት

ጳውሎስ በንጉሥ አግሪጳ ፊት። በኢየሱስ ክርስቶስ ምስክርነት ብርቱ፣ በዳንኤል ኤ. ልዊስ

አትም