መንፈሳዊ ትምህርት ቤት እና ኢኒስቲትዩት
በመንፈስ አስተምሩ


“በመንፈስ አስተምሩ፣” በአዳኙ መንገድ ማስተማር፦ በቤት እና በቤተክርስቲያን ውስጥ ለሚያስተምሩ ሁሉ [2022 (እ.አ.አ)]

“በመንፈስ አስተምሩ፣” በአዳኙ መንገድ ማስተማር

ምስል
አዳኙ በይሁዳ ምድረ በዳ

ልክ አዳኙ ለአገልግሎቱ በመንፈስ ለመዘጋጀት ጊዜ እንደወሰደው፣ እኛም በመንፈስ ለማስተማር እራሳችንን ማዘጋጀት አለብን።

በመንፈስ አስተምሩ

አዳኙ ጆሴፍ ስሚዝን እና ሲድኒ ሪግደንን የእርሱን ወንጌል እንዲሰብኩ ሲያዛቸው፣ እንዲህ ሲል ቃል ገባላቸው፣ “ለምትሉት ማንኛቸውም ነገሮች ሁሉ ምስክር ይሰጣችሁ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ ይላካል” (ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 100፥8፤ እንዲሁም ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 42፥15–1750፥17–22ይመልከቱ)። ወንጌልን ለሚያስተምሩ ሁሉ እናንተንም ጨምሮ ተመሳሳይ ቃል ኪዳን ተግባራዊ ይሆናል። የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል ስታስተምሩ፣ መንፈስ ቅዱስ ሊመራችሁ እና እውነታውን ለምታስተምሯቸው ሰዎች አእምሮዎች እና ልቦች ሊመሰክር አብሯችሁ ሊሆን ይችላል (ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 8፥2 ይመልከቱ)። ስታስተምሩ ብቻችሁን አይደላችሁም ምክንያቱም “የሚነግረው መንፈስ ቅዱስ ነው እንጂ እናንተ አይደላችሁምና” (ማርቆስ 13፥11)።

መንፈስ ቅዱስ ትክክለኛው አስተማሪ ነው። ማንኛውም ስጋ ለባሽ አስተማሪ ምንም ያህል የተካነ ወይም ልምድ ያለው ቢሆን፣ እውነታን በመመስከር፣ ስለክርስቶስ በመመስከር እና ልቦችን በመቀየር የእርሱን ሚና መጫወት አይችልም። ነገር ግን ሁሉም አስተማሪዎች የእግዚአብሔርን ልጆች በመንፈስ እንዲማሩ በመርዳት መሳሪያዎች መሆን ይችላሉ።

በመንፈስ ለማስተማር

  • በመንፈስ እራሳችሁን አዘጋጁ።

  • ተማሪዎቹ ስለሚያስፈልጓቸው ነገሮች መንፈሳዊ ሀሳቦችን ስታገኙ ምላሽ ለመስጠት ሁሌም ዝግጁ ሁኑ።

  • በመንፈስ ቅዱስ የሚማሩበትን ቦታ እና እድል ፍጠሩ።

  • ተማሪዎች የግል ራእይን እንዲሹ፣ እንዲያውቁ፣ እና ተግባራዊ እንዲያደርጉ አግዙ።

  • ብዙ ጊዜ ምስክርነታችሁን ስጡ፣ እናም ተማሪዎች ስሜታቸውን፣ ልምዳቸውን፣ እና ምስክርነታቸውን እንዲያካፍሉ ጋብዙ።

አዳኙ ለማስተማር እራሱን በመንፈስ አዘጋጀ

ለአገልግሎቱ ለመዘጋጀት ኢየሱስ “ከእግዚአብሔር ጋር ለመሆን” 40 ቀናትን በምድረ በዳ ውስጥ አሳለፈ (የጆሴፍ ስሚዝ ትርጉም፣ ማቴዎስ 4፥1 [በ ማቴዎስ 4፥1፣ የግርጌ ጽሁፍ ])። ነገር ግን የእርሱ መንፈሳዊ ዝግጅት የጀመረው ከረዥም ጊዜ በፊት ነበር። ሰይጣን ሲፈትነው “ለዛች ሰዓት” ያስቀመጣቸውን “የሕይወት ቃላት” ሊጠቀም ቻለ (ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 84፥85)። ለማስተማር እራሳችሁን በመንፈስ ለማዘጋጀት ስለምታደርጓቸው ጥረቶች አስቡ። በመንፈስ ዝግጅታችሁ ወቅት የአዳኙን ምሳሌ መከተል ስለምትችሉበት መንገድ ከ ማቴዎስ 4፥1–11 ምን ትማራላችሁ?

መንፈስ ትክክለኛ አስተማሪ እና የመለወጥ ትክክለኛ ምንጭ ነው። ኃይለኛ የወንጌል ትምህርት ዝምብሎ ትምህርትን ማዘጋጀት ብቻ ሳይሆን ነገር ግን ማስተማር ከመጀመራችሁ በፊት እራሳችሁን በመንፈስ ማዘጋጀትን ይጠይቃል። በመንፈስ ከተዘጋጃችሁ ስታስተምሩ የመንፈስን ምሪት የበለጠ ለመስማት እና ለመከተል ትችላላችሁ። በትምህርታችሁ ውስጥ መንፈስ ቅዱስን የመጋበዝ መንገድ እርሱን ወደ ሕይወታችሁ መጋበዝ ነው። ይህ የአዳኙን ምሳሌ በትጋት መከተልን እና ወንጌሉን በፍጹም ልባችሁ መኖርን ያካትታል። ማንኛችንም ይህን ፍፁም በሆነ ሁኔታ ማድረግ ስለማንችል፣ በተጨማሪም በየቀኑ ንስሃ መግባት ማለት ነው።

የማሰላሰያ ጥያቄዎች፦ ለማስተማር እራሳችሁን በመንፈስ ማዘጋጀት ማለት ለእናንተ ምን ማለት ነው? እራሳችሁን በመንፈስ የምታዘጋጁበትን መንገድ ለማሻሻል ምን ለማድረግ ትነሳሳላችሁ? መንፈሳዊ ዝግጅት በትምህርታችሁ ላይ ለውጥ ማምጣት ስለመቻሉ እንዴት ታስባላችሁ?

ቅዱሳት መጻህፍት ፦ መጽሐፈ ዕዝራ 7፥10ሉቃስ 6፥12አልማ 17፥2–3፣ 9ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 11፥2142፥13–14

አዳኙ ለሌሎች ሰዎች ፍላጎቶች ምላሽ ለመስጠት ሁሌም ዝግጁ ነበር

የምኩራቡ አለቃ ኢያኢሮስ በኢየሱስ እግር ፊት በመውደቅ እየሞተች ያለችውን ልጁን እንዲረዳት ተማፀነው። ኢየሱስ በድንገት በቆመ ጊዜ እርሱ እና ደቀ መዛሙርቱ ወደ ኢያኢሮስ ቤት ወደሚያመራው የተጨናነቀ ጎዳና ላይ እየሄዱ ነበር። “ማነው የነካኝ?” ብሎ ጠየቀ። የማይጠበቅ ጥያቄ ይመስል ነበር—በሰዎች ግርግር ውስጥ ማን ነበር የማይነካው? ነገር ግን አዳኙ በዚያ ግርግር ውስጥ የሆነ ሰው በለተየ ፍላጎት እና እምነት የሚሰጠውን ፈውስ ለመቀበል እንደቀረበው ተገነዘበ። የኢያኢሮስን ሴት ልጅ ለመጎብኘት አሁንም ሰዓት ይኖራል። ነገር ግን ልብሱን ለነካችው ሴት እንዲህ አላት፣ “ልጄ ሆይ፣ እምነትሽ አድኖሻል፣ በሰላም ሂጂ” ( ሉቃስ 8፥41–48ይመልከቱ)።

እንደ አስተማሪ አንዳንድ ጊዜ ለማስተማር የተዘጋጃችሁትን ለመጨረስ ስትቸኩሉ እራሳችሁን ልታገኙ ትችላላችሁ። ያ አስፈላጊ ሊሆን ቢችልም፣ በችኮላችሁ ሳታስቡት የምታስተምሩትን ግለሰብ አንገብጋቢ ፍላጎት አልፋችሁ አለመሄዳችሁን እርግጠኞች ሁኑ። ለማስተማር ስትዘጋጁ ከምትሹት መንፈሳዊ ምሪት በተጨማሪ፣ ስታስተምሩም የመንፈስ ምሪትን እሹ። የተማሪዎችን ፍላጎት፣ ጥያቄዎች እና ዝንባሌዎች ለማወቅ ሞክሩ። አንድ ተማሪ ያስተማራችሁትን እንዴት እንደተቀበለ ወይም እንደተገነዘበ እንድታስተውሉ መንፈስ ቅዱስ ሊረዳችሁ ይችላል። አንዳንዴ ዕቅዳችሁን እንድትቀይሩ ሊያነሳሳችሁ ይችላል። ለምሳሌ፣ አስባችሁት ከነበረው የበለጠ ብዙ ጊዜ በአንድ ርዕስ ላይ ማሳለፋችሁ ወይም አሁን ለተማሪዎች የበለጠ ጠቃሚ የሆነን ነገር ለማስቀደም የተወሰኑ ውይይቶችን ለወደፊት ማቆየታችሁ ሊገርማችሁ ይችላል።

የማሰላሰያ ጥያቄዎች፦ አንድ ወላጅ ወይም ሌላ አስተማሪ እንደተማሪ ያሏችሁን ፍላጎቶች እንደሚያውቅ መቼ ተሰምቷችሁ ያውቃል? የምታስተምሯቸው ሰዎች ትምህርቱን ከመጨረስ ይልቅ ፍላጎታችሁ እነሱ እንዲማሩ እንደሆነ ያውቃሉን? ፍላጎታችሁን በተሻለ ሁኔታ መግለፅ የምትችሉት እንዴት ነው?

ከቅዱሳት መጻህፍት፦ 1 ኛ ጴጥሮስ 3፥15አልማ 32፥1–940፥141፥142፥1

አዳኙ ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ እንዲማሩ እድሎችን ሰጠ

በኢየሱስ ጊዜ ለብዙ ሰዎች እርሱ በእውነት ማን እንደነበረ መረዳት ከባድ ነበረ፣ ነገር ግን ብዙ አስተሳሰቦች ነበሩ። ደቀመዛሙርቱ “አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ ሌሎችም ኤሊያስ፣ ሌሎችም ኤርሚያስ ወይም ከነቢያት አንዱ” ብለው መለሱ። ነገር ግን ኢየሱስ ደቀመዛሙርቱ የሌሎችን አስተያየት ወደ ጎን በመተው ወደገዛ ልቦቻቸው ውስጥ እንዲመለከቱ የሚጋብዝን ጥያቄ እንዲህ ጠየቀ፦ “እናንተስ እኔን ማን እንደሆንሁ ትላላችሁ?” መልሳቸውን “ከስጋ እና ደም” ሳይሆን፣ ነገር ግን በቀጥታ “ከሰማያት [ካ]ለው አባ[ት]” እንዲያገኙት ፈለገ። እንደዚህ ዓይነት ምስክርነት ነበር—ከመንፈስ ቅዱስ የሚመጣ የግል ራዕይ— ጴጥሮስን “አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ” ብሎ እንዲናገር ያደረገው ( ማቴዎስ 16፥13–17ይመልከቱ)።

በኋለኞቹ ቀናት በመንፈስ ለመዳን፣ የምታስተምሯቸው ሰዎች የእውነትን መንፈሳዊ ምስክርነት ይፈልጋሉ። እርሱን ለእነሱ መስጠት አትችሉም፣ ነገር ግን እንዲሹት መጋበዝ፣ ማበረታታት፣ ማነሳሳት እና ማስተማር ተችላላችሁ። በቃላችሁ እና በተግባራችሁ አማካኝነት መንፈስ ቅዱስ ለወንጌል ትምህርት እንዴት አስፈላጊ እንደሆነ ግልፅ ማድረግ ትችላላችሁ። ለምሳሌ፣ ስለምትፈጥሩት እና ስለምታበረታቱት የትምህርት ሁኔታ አስቡ። በክፍል ውስጥ የወንበሮችን አቀማመጥ ወይም ለተማሪዎች ሰላምታ የምትሰጡበት እና መስተጋብር የምትፈጥሩበት መንገድ የመሳሰሉ ቀላል ነገሮች ተማሪዎች ለሚኖራቸው ልምድ መንፈሳዊ መድረክ ይፈጥራል። እናንተ ለማስተማር በመንፈስ እንደምትዘጋጁት ሁሉ ተማሪዎች እራሳቸውን ለመማር በመንፈስ እንዲያዘጋጁ መጋበዝም ትችላላችሁ። ለሚያመጡት መንፈስ ሃላፊነትን እንዲወስዱ ጠይቁ። እናም መንፈስ ስለኢየሱስ ክርስቶስ እና ስለወንጌሉ ሲመሰክር እንዲሰማቸው ለእነሱ እድሎችን መስጠት ትችላላችሁ። ያ ምስክርነት ለእነሱ እንደ “አለት” ይሆናቸዋል “የገሃነም ደጆችም አይች[ላቸውም]” (ማቴዎስ 16፥18)።

የማሰላሰያ ጥያቄዎች፦ ለወንጌል ትምህርት መንፈሳዊ ሁኔታ አስተዋጽዖ የሚያደርግ ምን ነገር ተገንዝባችኋል? የእሱን መገኘት የሚቀንሰውስ ምንድን ነው? የምታስተምሯቸው ሰዎች ከመንፈስ እንዲማሩ ምን ሊረዳቸው ይችላል? ብዙ ጊዜ የምታስተምሩበትን ቦታና ሁኔታ አስቡ። እዚያ ስትሆኑ ምን ይሰማችኋል? መንፈስ እዚያ እንዲገኝ እንዴት በተሻለ ውጤታማነት መጋበዝ ትችላላችሁ?

ከቅዱሳት መጻህፍት፦ ሉቃስ 24፥31–32ዮሐንስ 14፥2616፥13–15ሞሮኒ 10፥4–5ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 42፥16–1750:13–24

ምስል
ሚስዮናውያን ቤተሰብን ሲያስተምሩ

ስናስተምር ተማሪዎች የራሳቸውን የእውነት መንፈሳዊ ምስክርነት እንዲሹ መጋበዝ እንችላለን።

አዳኙ ሌሎች ሰዎች ግላዊ ራዕይን እንዲሹ፣ እንዲገነዘቡ እና ተግባራዊ እንዲያደርጉ አገዛቸው

ጌታ ከእኛ ጋር መነጋገርን ይፈልጋል እንዲሁም ከእኛ ጋር እየተነጋገረ እንዳለ እንድናውቅ ይፈልጋል። በ1829 (እ.አ.አ)፣ ኦሊቨር ካውደሪ የተባለ የ22 ዓመት የትምህርት ቤት አስተማሪ ማንም ሰው ግላዊ ራዕይን መቀበል እንደሚችል የሚገልፀውን አስደሳች ትምህርት እየተማረ ነበር። ነገር ግን ብዙዎቻችን ከጠየቅናቸው ተመሳሳይ የሆኑ ጥያቄዎች ነበሩት “በእርግጥ ጌታ ለእኔ ለመናገር እየሞከረ ነውን? እና ምን እየተናገረ እንዳለ እንዴት ማወቅ እችላለሁ?” እነዚህን ጥያቄዎች ለመመለስ ኢየሱስ ክርስቶስ ኦሊቨርን ስለጥልቅ መንፈሳዊ የምርምር ጊዜ ወደኋላ ተመልሶ እንዲያስብ ጋበዘው። “ለአእምሮህ ሰላምን አልተናገርኩኝምን?” ብሎ ጠየቀ ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 6፥21–24ይመልከቱ)። ከዚያም መንፈስ ሊናገር ስለሚችልባቸው ሌሎች መንገዶች ኦሊቨርን አስተማረው ( ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 8፥2–39፥7–9፤ እንዲሁም ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 11፥12–14ይመልከቱ)።

መንፈሳዊ ነገሮችን ብዙ ጊዜ ችላ በሚል ዓለም ውስጥ በመኖራችን፣ ሁላችንም የመንፈስን ድምፅ የመገንዘብ እርዳታን እንሻለን። ሳንገነዘበው መንፈስ ተሰምቶን ሊሆን ይችላል። እናም ሁላችንም እንዴት መንፈስን መሻት፣ ተፅዕኖዎቹን መገንዘብ እና በሚሰጠን መነሳሳት ላይ ተግባራዊ እርምጃ መውሰድ እንደምንችል መማር እንችላለን። ስታስተምሩ መንፈስ የሚናርበትን መንገዶች እና እንዴት ከእነሱ ጋር እንደተነጋገረ እንዲያውቁ ተማሪዎችን አግዙ። እንደአስተማሪ ከምትሰጧቸው ታላቅ ስጦታዎች ውስጥ አንዱ የምታስተምሯቸውን ሰዎች በዚህ የእድሜ ልክ ግላዊ ራዕይ ፍለጋ ሂደት መርዳት ነው።

የማሰላሰያ ጥያቄዎች፦ግላዊ ራዕይን ስለመቀበል መማር አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው? ራዕይን እንዴት እንደምትሹ እና እንደምትገነዘቡ የሆነ ሰው እረድቷችሁ ያውቃልን? የምታስተምሯቸው ሰዎች ከመንፈስ ቅዱስ የሚያመጣን ራዕይ እንዲሹ፣ እንዲገነዘቡ እና ተግባራዊ እንዲያደርጉ እንዴት ማበረታታት ትችላላችሁ።

ከቅዱሳት መጻህፍት፦ ገላትያ 5፥22–23አልማ 5፥45–47ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 42፥61121፥33ጆሴፍ ስሚዝ ታሪክ 1፥8–20

አዳኙ ላስተማራቸው ሰዎች ምስክርነትን ሰጠ

በደግነት በማስተማር እና በማገልገል የተለየ ወቅት ኢየሱስ ወንድሟ የሞተባትን ማርታን ለማፅናናት ፈለገ። ስለዘላለማዊ እውነት ቀላል ምስክርነትን አካፈላት፦ “ወንድምሽ ይነሳል” (ዮሐንስ 11፥23)። የእርሱ ምስክርነት የራሷን ምስክርነት እንድታካፍል ማርታን አነሳሳት፦ “በመጨረሻው ቀን በትንሳኤ እንዲነሳ አውቃለሁ” (ዮሐንስ 11፥24)። ይህ ክስተት በ ዮሐንስ 11፥25–27 ውስጥ እንዴት እንደተደገመ አስተውሉ። ስለ አዳኙ ምሳሌ ምን ያስደንቃችኋል? የወንጌል እውነቶችን ምስክርነት ማካፈል የማስተማር አስፈላጊ አካል የሆነው ለምንድን ነው ?

ምስክርነታችሁ በምታስተምሯቸው ሰዎች ላይ ኃይለኛ ተፅዕኖ ሊያሳድር ይችላል። ምስክርነታችሁ አንደበተ ርቱዕ ወይም ረዥም መሆን የለበትም። እንዲሁም “ምስክርነቴን ማካፈል እፈልጋለሁ” በማለት መጀመር የለበትም። በቀላሉ የምታውቁትን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል አካፍሉ። የእውነት ምስክርነት ቀጥታ እና ከልብ ሲሆን በጣም ኃይል አለው። ስለአዳኙ፣ ስለወንጌሉ እና በሕይወታችሁ ውስጥ ስላለው የእርሱ ኃይል በተደጋጋሚ መስክሩ እንዲሁም የምታስተምሯቸው ሰዎች ተመሳሳይ ነገር እንዲያደርጉ አበረታቷቸው። እናም አንዳንድ ጊዜ በጣም ኃይለኛ ምስክርነት የሚሰጠው በአስተማሪው ሳይሆን በተማሪው እንደሆነ አስታውሱ።

የማሰላሰያ ጥያቄዎች፦ አንድ ሰው ምስክርነት በማካፈል የሚያሳድረውን ኃይለኛ ተፅዕኖ የሚገልፁ ምሳሌዎችን በቅዱሳት መጻህፍት ውስጥ ፈልጉ። ከነዚያ ምሳሌዎች ምን ትማራላችሁ? በሌላ ሰው ምስክርነት ተባርካችሁ የነበረው መቼ ነው? ምስክርነታችሁን ማካፈላችሁ በምታስተምሯቸው ሰዎች ላይ ተፅዕኖ ያሳደረው እንዴት ነው? እናንተ ላይ ተፅዕኖ ያሳደረው እንዴት ነው?

ከቅዱሳት መጻህፍት፦ የሐዋርያት ስራ 2፥32–38ሞዛያ 5፥1–3አልማ 5፥45–4818፥24–4222፥12–18ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 46፥13–1462፥3

የምትማሩትን ነገር ተግባራዊ የምታደርጉባቸው አንዳንድ መንገዶች

  • ተማሪዎች የእግዚአብሔርን ቃል ሲያጠኑ መንፈስ ቅዱስ ምን እንዳስተማራቸው እንዲያካፍሉ ጠይቋቸው።

  • ስታስተምሩ መንፈሳዊ መነሳሳትን ለመቀበል ቀደም ብላችሁ ተዘጋጁ።

  • ስትዘጋጁ የሚመጡትን መንፈሳዊ ግፊቶች ፃፉ።

  • መንፈስ ቅዱስ የሚያስተምራቸውን ነገር በፀጥታ እንዲያሰላስሉ ለክፍል አባሎች አልፎ አልፎ እድሎችን ስጡ።

  • የመንፈስ ተፅዕኖዎችን ለመጋበዝ ቅዱስ መዝሙርን እና ፎቶዎችን ተጠቀሙ።

  • ዕቅድ ስታወጡ እና ስታስተምሩ መነሳሳትን አዳምጡ እንዲሁም ዕቅዶቻችሁን ለማስተካከል ፍቃደኞች ሁኑ።

  • ስለሚማሩት ነገር ምስክርነታቸውን እንዲሰጡ ለሁሉም ተማሪዎች እድሎችን ስጡ።

  • መንፈስ በቦታ ሲገኝ መገንዘብ እንዲችሉ ሌሎችን እርዱ።

  • የምታስተምሯቸውን እውነታዎች መመስከር እንድትችሉ ኑሯቸው።

  • በድንገተኛና መደበኛ ባልሆኑ ወቅቶች ለማስተማር መነሳሳቶችን ተከተሉ።

አትም