2010–2019 (እ.አ.አ)
ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ተመልከቱ
የሚያዝያ 2019 (እ.አ.አ) አጠቃላይ ጉባኤ


ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ተመልከቱ

ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ከተመለከትን እንደ እስራኤል ሽማግሌዎች ቃለኪዳናችንን እንድንጠብቅ እና ጥሪያችንን እንድናጎላ ይረዳናል፡፡

ኢየሱስ በቅፍረናሆም አቅራቢያ በሚገኘው መንገድ ላይ በብዙ ሰዎች ተከቦ ሲራመድ፤ በጠንካራ ህመም ለ አስራ ሁለት አመት ስትሰቃይ የነበረች ሴት ቀርባ የልብሱን ጫፍ ዳሰሰች፡፡1 እሷም ወድያው ተፈወሰች፡፡2

ቅዱሳን መፀሐፍ ኢየሱስ‹‹ከእርሱ፤ ‹‹ኃይል እንደወጣ በገዛ እራሱ አውቆ››3 ‹‹በሕዝብ መካከል ዘወር ብሎ››4 ‹‹ይህንም ያደረገችውን ለማየት››5 ‹‹ሴቲቱ ግን የተደረገላትን ስላወቀች፣እየፈራች እየተንቀጠቀጠች››6 ‹‹መጥታ በፊቱ ተደፍታ እውነቱን ሁሉ ነገረችው፡፡››7

“እርሱም። ልጄ ሆይ፥ እምነትሽ አድኖሻል፤ በሰላም ሂጂ አላት” ።8

ኢየሱስ ክርስቶስ ሴትየዋን አዳናት አካላዊ ፈውስ አድርጎላት ነበር፤ ኢየሱስ ሊያያት ሲዞር፤ በእርሱ ላይ ያላትን እምነት አወጀች እርሱ ደግሞ ልቧን ፈወሰው፡፡ 9 በፍቅር አናገራት ፤ የእርሱን ይሁንታ አረጋገጠላት ፤እና በእርሱ ሰላም ባረካት 10

ወንድሞች እንደ ቅዱስ ክህነትን ተሸካሚነታችን፤ ሁላችንም በደህንነት ስራ ላይ ተሳታፊ ነን፡፡ በመጨረሻው አመታት ጌታ የስራውን ኃላፊነት በእስራኤል ሽማግሌዎች ትከሻ ላይ እኩል አድርጎ አስቀምጧል11 ጌታ የሚያበረታታ ሀላፊነት ሰጥቶናል- ከእህቶቻችን ጋር ስንሰራ፣ በተቀደሰ መንገድ እንድናገለግል፣ በሁለቱም መጋረጃ በኩል የእስራኤልን መሰባሰብ ማፋጠን፤ቤታችንን የእምነት መገኛ እና የወንጌል መማሪያ አድርገን ማቋቋም፤ እንዲሁም አለምን ለኢየሱስ ዳግም ምፅአት እንድናዘጋጅ፡፡ 12

አዳኛችን የሁሉ ነገር መንገድን እንደማሳየቱ መጠን፤እርሱም ወደ አባቱን ያይ እና ያገለግለው እንደነበር እኛም ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ መመልከት እና እርሱን ማገልገል አለብን፡፡ 13 አዳኛችን ለነብዩ ጆሴፍ በዚህ መንገድ ነበር የተናገረው፡፡

“ባሰባችሁት ነገር ሁሉ ወደ እኔ ተመልከቱ፣ አትጠራጠሩ፣ አትፍሩ፡፡

ጎኔ ላይ የተወጋሁት ቁስል፣ እናም በእጄ እና በእግሬ ላይ ያሉትን የምስማር ምልክቶች አስቧቸው፤ እናም እምነት ይኑራችሁ፣ ትእዛዛቴን ጠብቁ፣ እናም መንግስተ ሰማያትን ትወርሳላችሁ።14

በቅድመ ዓለም ግዛት ኢየሱስ ለአባቱ እንዲ ብሎ ቃልኪዳን ገብቷል፤ የአባቱን ፍቃድ ሊፈፅም ፤ አዳኛችን እና ቤዛችን ሊሆን፡፡ አባቱም ‹‹ማንን እልካለሁ? ›› ብሎ በጠየቀ ወቅት፡፡15 ኢየሱስም እንዲህ ሲል መለሰ፤

“ይሄው እዚህ ነኝ፣እኔን ላከኝ።”16

“አባት ሆይ፣ ፈቃድህ ይፈጸም፣ እናም ክብርም ለዘለአለም ያንተ ይሁን።”17

በመላው የምድር ህይወቱ ኢየሱስ ያንን ቃልኪዳን ኖሮታል፡፡ በትህትና፤በርህራሄ እና በፍቅር አባቱ በሰጠው ኃይልና ስልጣን አማካኝነት የአባቱን ትምህርት አስተማረ የአባቱንም ስራ ሰራ፡፡ 18

ኢየሱስ ልቡን ለአባቱ አሳልፎ ሰጥቶል እንዲህም አለ፧

‹‹አብን እንድወድ››19

‹‹አብም እንዳዘዘኝ እንዲሁ አደርጋለሁ››20

‹‹ፈቃዴን ለማድረግ አይደለም እንጂ የላከኝን ፈቃድ ለማድረግ ከሰማይ ወርጃለሁና፡፡››21

እየተሰቃየ በጌቴስማኒ ‹‹ነገር ግን ፤የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ እንጂ›› እያለ ይጸልይ ነበር፡፡22

ጌታ እስራኤል ላሉ ሽማግሌዎቹ በጠራቸው ግዜ ‹‹ወደ እኔ በሁሉም በኩል እዩ›› እና ‹‹ቁስሎቹን ›› ከሞት የተነሳውን አካሉን፤ ከሃጥያት መመለሻ ጥሪ እና ከዓለም እና ወደ እርሱ መመለስ እና እሱን መውደድ እና መታዘዝ ነው፡፡ ይህ ጥሪ ትምህርቱን በእርሱ መንገድ እንድናስተማር እና ስራውን በእርሱ መንገድ እንድንፈፅም ነው፡፡ ስለዚህ ፤ ይሄ ፤እርሱን በፍፁም እንድናምነው፤ ፍቃዳችንን ለእርሱ አሳልፈን እንድንሰጠው እና ልባችንን ለእርሱ እንድንማርክ፤ እናም በእርሱ የማዳን ኃይል እርሱን እንድንመስል ጥሪ ነው፡፡23

ወንድሞች፤ ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ከተመለከትን በእስራኤል ውስጥ ሽማግሌዎቹ እንድንሆን ይባርከናል- ትሁት፣ሩህሩህ፣ የተሰጠን፤ የእርሱ ፍቅር የሞላን፡፡24 እናም የወንጌሉን በረከት እና ደስታ እና ቤተክርስቲያን ለቤተስባችን እና ከመጋረጃው በሁለቱም በኩል ላሉትን ለወንድምቻችን እና ለእህቶቻችንን እናመጣለን ፡፡

ፕሬዝዳንት ራስል ኤም ኔልሰን ወደ ኢየሱስ ክርሰቶስ በዚህ መልኩ እንድናይ ጠርተውናል‹‹ጠንኳራ ሀዋርያ ለመሆን ቀላል ነገር ወይም የሚያቀል ነገር የለም ››። አትኩሮታችን መሆን ያለበት በአዳኛችን እና በእርሱ ወንጌል ላይ መታስር ነው፡፡ በሁሉም አስተሳሰባችን ወደ እርሱ እንድንመለከት ማድረግ አእምሮን ማጠንከርን ይጠይቃል፡፡ ነገር ግን እንደዛ ስናደርግ፤ ጥርጣሬያችን እና ፍርሀታችን ይጠፋል፡፡25

‹‹መጣበቅ›› ታላቅ ቃል ነው፡፡ ትርጉሙም በጥንካሬ መታሰር፣ መሳሳብ እና በፍፁም መያዝ ማለት ነው፡፡26 ቃልኪዳናችንን በመጠበቅ አትኩሮታችንን በኢየሱስ ክርስቶስ እና በወንጌሉ ላይ እናስራለን

ቃልኪዳችንን መጠበቅ በሁሉም ስራዎቻችን እና በንግግራችን ላይ ተፅእኖ ይኖረዋል ፡፡ የምንኖረው የቃልኪዳን ህይወት 27 በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ያተኮሩ ሙሉ ቀላል የቀን በቀን የእምነት ተግባሮች፤ ከልብ የመነጨ ፀሎት በእርሱ ስም፤ የእርሱንቃል መመገብ፤ ለሃጥያታችን ንስሀ ለመግባት ወደ በእርሱመዞር፤የእርሱን ትዛዛት መጠበቅ፤ ቅዱስ ቁርባን መውሰድ እና የእርሱንቀድሶ መጠበቅ፤ በተቀደሰውየእርሱ ቤተ መቅደሱ በቻልነው መጠን ማምለክ፤ እና ቅዱሱን የእርሱን ክህነት የእግዚአብሔርን ልጆች ለማገልገል መለማማድ ነው፡፡

ቃልኪዳኖቻችን በመሰጠት ስንወጣ ልባችንን እና አእምሮአችንን ለአዳኛችን የቤዛነት ኃይል እና በመንፈስ ቅዱስ ቅድስና ተፅእኖ ስር እንሆናለን፡፡ አዳኛችን የእኛን ተፈጥሮ መስመር በመስመር ይቀይራል፤ ወደ እርሱ በጥልቅ ይለውጠናል እናም ቃልኪዳናችን በልባችን ውስጥ ህይወትን ይዘራል፡፡28

ለሰማይ አባታችን የምንገባው ቃል ጠንካራ ቆራጥነት እና፤ የውስጣችን ጥልቅ ፍላጎትን ያሳያል፡፡ የሰማይ አባታችን የገባልን ቃልኪዳኖች በምስጋና እና በደስታ ይሞሉናል፡፡29 ቃልኪዳኖቻችን የምንከተላቸው ህጎች መሆናቸው ይቀርና የምንወዳቸው የሚያነሳሱን፤ የሚመሩን እናም አትኩሮታችንን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ እንድናጣብቅ የሚረዱን መርሆች ይሆናሉ፡፡ 30

ይህ የቆራጥነት ተግባር ለሁሉም ፤ ለወጣት እና ለአዛውንት አለ፡፡ እናንት ወጣት ወንዶች ቅዱስ የሆነውን የአሮናዊውን ክህነት የተሸከማችሁ፤ በዚህ ምሽት የምለው ሁሉ በእናንተ ይተገበራል፡፡ ስለ እናንተ እግዚአብሔርን አመስግናለሁ ፡፡ እናንተ ቅዱስ የሆነውን ስርዐት እና ቃልኪዳን ለሚሊዮን የኋለኛው ቀን ቅዱሳን በሳምንቱ ታቀርባላችሁ፡፡ ቅዱስ ቁርባኑን ስታዘጋጁ፣ስትባርኩ ወይም ስታሳልፉ፤ ስታገለግሉ፤ በቤተ መቅድስ ስታጠምቁ፤ ጓደኞቻችሁን ወደ መነቃቅያ ዝግጅቶች ስትጋብዙ ወይም የጉባኤ አባሎቻችሁን ስታድኑ፤ የደህንነተ ስራን እየፈፀማችሁ ነው፡፡ እናንተም ወደ የኢየሱስ ክርስቶስ መመልከት እና በየቀኑም ቃልኪዳኖቻችሁን መኖር ትችላላችሁ፡፡ ቃል እገባላችኋለሁ ይህን ካደረጋችሁ፣ አሁን እና በመጭው ቀናት፣ የእስራኤል ብርቱ ሽማግሌዎች፣ የጌታ ታማኝ አገልጋዮች ትሆናላችሁ፡፡

ወንድሞቼ አውቃለሁ ይህ ሁሉ ከባድ ይመስላል፡፡ ግን እባካችሁ የአዳኛችንን እነዚህን ቃላቶች አስታውሱ ‹‹አብ ከእኔ ጋር ስለ ሆነ ብቻዬን አይደለሁም››፡፡31 ለእኛም ቢሆን እንዲሁ ነው። ብቻችንን አይደለንም። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እና የሰማይ አባታችን ይወዱናል፤ እና ከእኛ ጋር ናቸው፡፡32 ምክንያቱም ኢየሱስ ወደ አባቱ ተመልክቶ ታላቁን የስርየት መስዋትነት አጠናቅቆአል፤ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚረዳን እርግጠኛ በመሆን ወደ እሱ መመልክት እንችላለን፡፡

ማንኛችንም ፍጹም አይደለንም፤ አንዳንዴ ወደ ኋላ እንቀራለን ፡፡ ተስፋ እንቆርጣለን ሀሳባችን ይበታተናል ፡፡ እንደናቀፋለን፡፡ ነገር ግን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ በንስሃ ልብ ከተመለከትን እሱ ወደ ላይ ከፍ ያደርገናል፤ ከሃጥያት ያነፃናል፤ ይቅር ይለናል እና ልባችንን ይፈውሰዋል ፡፡ እርሱ ታጋሽ እና ደግ ነው፡፡ የእርሱ የማዳኛ ፍቅሩ በፍፁም አያልቅም እና በፍፁም አይወድቅም፡፡33 እንደ እስራኤል ሽማግሌዎች ቃለኪዳናችንን እንድንጠብቅ እና ጥሪያችንን እንድናጎላ ይረዳናል፡፡

አላማው አንዲሳካ ፤አብ በአስፈላጊ ነገሮች ሁሉ ይባርከናል፡፡‹‹በመሆኑም፣ ፤ በሰማይ እናም በምድር በልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ አብ ፈቃድ የተላኩ ነገሮች ሁሉ፣ ህይወት እና ብርሀን፣ መንፈስ እና ሀይል፣ ለእርሱ ተገዢ ናቸውና።››34

መለኮታዊው ብርሃን እና ኃይል በህይወታችን ሲወርድ ሦስት ተአምራዊ ነገሮች ይከሰታሉ፡-

በመጀመሪያ፤ማየት አንችላለን ከውጭ ባለፈ ጥልቅ ልብን ኢየሱስ ሴቲቱን እንዳያት በራዕይ አማካኝነት እኛም ማየት እንጀምራልን፡35 ኢየሱስ የእንደሚያየው ስናይ ፤ በእርሱ ፍቅር የምናገለግላቸውን እንድንወዳቸው ይባርከናል፡፡ በእርሱ እርዳታ፤ እኛ የምናገግላቸው አዳኛችንን ያዩታል እና ፍቅሩም ይስማቸዋል፡፡ 36

ሁለተኛ፤ የክህነት ኃይል አለን፡፡ ለመባረክ፤ ለመምራት፤ለመጠበቅ፤ ለማጠንከር እና ሌሎችን ለመፈወስ እና ለእነሱ ለምንወዳቸው ታምራትን ለማምጣት እና ቤተስባችንን እና ጋብቻችን በደህና ለመጠበቅ ይህንን ሁሉ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ለመስራት ስልጣን እና ኃይል አለን፡፡37

ሦስተኛ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ከእኛ ጋር ይሄዳል፤ በምንሄድበት ይሄዳል፤ ስናስተምር ያስተምራል፤ ስናፅናና ያፅናናል፡፡ ስንባርክ፤ ይባርካለ38

ወንድሞች፤ልንደሰትባቸው የሚገቡ ምክንያቶች የሉንምን? አለን; የእግሒአብሔርን ቅዱሱን ክህነት ይዘናል፡፡ ወደ ኢየሱስ ክርሰቶስ ስንመለከት፤ ቃልኪዳናችንን ስንኖር፤ እናም ትኩረታችንን እርሱ ላይ ስናጣብቅ፤ ከእህቶቻችን ጋር በጋራ እና በቅዱስ መንገድ ስናገለግል፤ በመጋረጃው በሁለቱም በኩል የተበተኑትን እስራኤል እንሰበስባለን፤ ቤተሰቦቻችንን እናጣምራለን እናም እናጠነክራለን፤ እናም አለምን ለጌታ ለኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምፅአት እናዘጋጃለን፡፡ ይህ ይሆናል፡፡ ስለዚህም እመሰክራለሁ።

በዚህ ከልብ የመነጨ ፀሎት እጨርሳለሁ፤ሁላችንም፤ እያንዳንዳችን; በሁሉም አመለካከታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ እንመልከት፡፡ አትጠራጠሩ፡፡ አትፍሩ፡፡ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም፣ አሜን።

ማስታወሻዎች

  1. ጄምስ ኢ. ታልሜጅ ይህ ፈውስ ሲካሄድ ኢየሱስን በቅፍረናሆም አካባቢ አስቀማጦት ነበር (see Jesus the Christ [1916], 313).

  2. ሉቃስ 8:43–44 ይመልከቱ፤ በተጨማሪ ማቴዎስ 9፡20–21ማርቆስ 5፥25–29፣ ን ይመልከቱ

  3. ሉቃስ 8፤46

  4. ማርቆስ 5፥30።

  5. ማርቆስ 5፥32።

  6. ሉቃስ 8፥47

  7. ማርቆስ 5፥33።

  8. ሉቃስ 8፥48

  9. ጄምስ ኢ ታልሜጅ እንደፃፈው ለሴቲቷ ከአካላዊ ፈውስ ባለፈ ትልቅ ዋጋዋ አዳኛችን የልቧን ምኞት ማሳካቱ ፤ እና እምነቷ በእርሱ ተቀባይነት ማግኘቱ ነው (ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ318 ይመልከቱ።)፡፡ ኢየሱስ አካሏንም፤ መንፈሷንም ፈወሰው እና የደህንነትን እቅድ መንገድን ከፈተላት፡፡

  10. ይሄ ፈውስ ሲሆን የሙክራቡአለቃ ኢያኢሮስ ከኢየሱስ ጋር እንደ ነበር ይታወቃል፡፡ ኢየሱስ የኢያኢሮስን የሙክራቡን አለቃ ልጅ ከሞት ለማስነሳት ወደ ኢያኢሮስ ቤት እያመራ ነበር፡፡ ኢየሱስ የፈወሳት ሴት ከሚክራቡ ባላት ችግር የተነሳ ተባራለች፡፡ ኢየሱስ ሴቲቱን ሲፈውሳት፤ ለሁሉም ኢያኢሮስን ጨምሮ፤ እስዋ ውድ ልጅ እንደሆነች፤ እምነት ያላት ሴት እናም በመንፈስ እና በአካል ሙሉ እንደሆነች ግልፅ አድርጎል፡፡

  11. See D. Todd Christofferson, “The Elders Quorum,” (Ensign or Liahona, May 2018, 55–58) for a discussion of the adjustments to create one Melchizedek Priesthood quorum in a ward. የለውጡ ምክንያት በሚኒስተሪነግ ድህረ ገፅ ተደጋጋሚ ጥያቄቆች ክፍል ተብራርቶአል ‹‹በአንድ ዋርድ ውስጥ አንድ የመልከፀዲቅ ክንከት ቸሸንጎ መኖሩ፤ የክህነት ተሸካሚዎች ሁሉንም የማዳን ስራ በአንድነት ተግባራሚ እንዲያደርጉ ይረዳቸዋል፤ከዚህ በፊት በሊቀካህን ቡድን መሪ ሲቀናበር የነበረውን የቤተመቅደስ እና የቤተሰብ ታሪክን ያካትታል›› (”This Is Ministering: Frequently Asked Questions,” 8, ChurchofJesusChrist.org/ministering).

    እነዚህ ለውጦች የዋርድ ሚሺን መሪውን; አዲሱን የቤተመቅደስ እና የቤተሰብ ታሪክ መሪዎችን በክህነት ፐሬዝዳንት መሪሞች ምሪት ስር አድርጎአችዋል፡፡ ለማሰተካከያውን የወሰዱት የደህንነት ስራ የሚሰሩት በሽማግሌ ጉባኤ መሪዎች በዚህ የአገልግሎት በነሱ ምሪት ለቤተስብዎችን ይገለገላሉ፡፡ በእርግጠኛነት፤ ኢጵስ ቆጶሱ በዋርዱ ወስጥ የደህንነትን ስራ የመስራተ ቁልፉን ይዘዋል፤ ቢሆንም እርሱ ይህንን ኃላፊነት እና ስልጣን ለሽማግላ ጉባኤ መሪው እንዲስራው ውክልና ይሰጠወአል ምክንያቱም ኢጲስ ቆጶሱ ከእራሱ ቤተስቦች ጋር የበለጠ ጊዜ እንዲያሳልፍ ፤ወጣቶችን እያጠነከረ እና በእስራኤል ውስጥ እንደ ዳኛ ሆኖ እንዲያገለግል፡፡

  12. ራስል ኤም.ኔልሰንን ተመልከቱ, “ሁላችንም ክፍት እንሁን,” Liahona, ግንቦት 2018, 118–19 ; ራስል ኤም.ኔልሰን, “ምሳሌያዊ አባል መሆን,” Liahona, ኅዳር. 2018, 113–14; ኩዊንተን ኤል. ኩክ, “Deep and Lasting Conversion to Heavenly Father and the Lord Jesus ChristLiahona ኅዳር . 2018, 8–12.

  13. እግዚአብሔር ውድ ልጁን፣ ኢየሱስ ክርስቶስን፣ ወደ አለም ላከ (ዮሀንስ 17፥18 ተመልከቱ)።

  14. ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 6፥36-37

  15. አብርሐም 3፥27።

  16. አብርሐም 3፥27።

  17. ሙሴ 4፥2

  18. ኢየሱስ የአባቱን ስራ ስለመስራቱ እና የአባቱን ትምህርት ስለማስተማሩ ፤በብዙ የሚቆጠሩ የቅዱሳነ መፀሐፍ ማጣቀሻዎች አሉ፡፡ ተመልከት ለምሳሌ የይሐንስ ወንጌል5:19(ኢየሱስ አብ ሲያደርግ ያየውን ያደርጋል።); የይሐንስ ወንጌል5:36(አብ ለልጅ የሚሰራ ስራ ሰጠው); የይሐንስ ወንጌል 8:26(ኢየሱስ ክአባቱ የተቀበለውን አስተምራል።); የይሐንስ ወንጌል 14:28(ኢየሱስ እንዲ አውጃል ‹‹ከእኔ አብ ይበልጣልና››); 3ኛ ኔፊ11:32(የእሱ ትምህርት አብ የሰጠው ትምህርት ነው።)

  19. ዮሐንስ 14፥31።

  20. ዮሐንስ 8፥29።

  21.  ዮሀንስ 6፥38፤ ደግሞም ዮሀንስ 5፥30

  22. ሉቃስ 22፥42

  23. ተመልከት የሚለው ቃል በዚህ አንቀፅ ውስጥ ማየትትምህርትና ቃልኪዳን 6:36–37 ከእግዛብሄር ጥሪ ጋር የሚስማማ ትርጉም አለው (መመለስ) ፤ አንድን ሀሳብ አቀጣጫ ማስቀየር፤ መደገፍ፤መፈለግ፤ በተስፋ መጠበቅ፤እንደመጨረሻማሰብ፤ መጠበቅ ወይም ተስፋ ማድረግ፡፡( see “Look,” Merriam-Webster.com).

  24. ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 121፥41–©42 ተመልከቱ። ቅዱሳን መፀሀፍት ላይ የክርስቶስ ባሃሪያት የምንላቸው በኢየሱስ ክርስቶስ ምህረት እና ፀጋ የሚመጡ የመንፈስ ስጦታዎች ናቸው፡፡ ያ ነው በእስራኤል ያሉትን ሽማግሌዎች ሽማግሌዎች የሚያደርጋቸው፡፡

  25. ራስል ኤም. ኔልሰን፣“የኢየሱስ ክርስቶስን ሀይል ሂወታችን ውስጥ መሳል”ሊሀይኦና ግንቦት 2017 (እ.አ.አ)፣ 41።

  26. merriam-webster.com, “rivet.”ተመልከት

  27. የቃልኪዳን ህይወት ስለሚለው ጽንሰ-ሀሳብ ውይይት ዶናልድ ኤል. ሄልስቶርምን ተመልከቱ, “የቃልኪዳን ሂወት መኖር,” Ensign, ሰኔ 2013, 46–49. ይሄ ጹሁፍ የተወሰደው ከ BYU–Idaho በ ግንቦት 2011 ከርጂም ንግግር የተወሰደ ነው፡፡ ረጂሙን ንግግርከ ከዶናልድ ኤል. ሄልስቶርምን ተመልከቱ, “የቃልኪዳን ሂወት ,“ ሰኔ ማክሰኞ ፣ ሜይ 10 ቀን 2011// (BYU–Idaho devotional, May 2011), web.byui.edu/devotionalsandspeeches/speeches.aspx.

  28. ጌታ አዲስ ቃልኪዳን ከ እስራኤል ቤት ጋር በልባቸው እንደሚጽፍ.የሚያውጅበ ትንቢተ ኤርሚያስ 31:31–33 ተመልከቱ። ቃልኪዳኑን በልባችን ስለመቅረጽ ጳውሎስ ጹሁፎች ላይ ይገኛል (2 ቆሮንቶስ 3:3; ዕብራዊያን 8:10 ተመልከት ።) ዴቪድ ኤ.ቤድናር፣ “በእግዚሀብሄር መለወጥ፣” Liahona፣ ኅዳር. 2012፣106–109።

  29. ለዳቦው የሚፀለየው የቅዱስ ቁርባን ፀሎት ከሰማይ አባታችን ጋር ያለንን የቃልኪዳናችንን ተፈጥሮአዊ ግንኙነት በቆንጆ ሁኔታ ይገልፀዋል፡፡ በአባታችን የመዳን እቅድ ከሰማይ አባታችን ጋር ቃልኪዳን ገብተናል፤ የገባናቸውን ቃልኪዳኖች ስንተገብር ቃልለተገባልን በረከቶት በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት ብቁ እንሆናለን፡ እርሱ አማላጅ ነው፡፡ በቅዱስ ቁርባን ስርአት ውስጥ፣(በውጤት ከሱጋር ቃልኪዳን በመግባት) የልጁን ስም በላያችን ላይ ለመውሰድ እና ሁሌም እርሱን ለማስታወስ እናም የሰጠንን ትእዛዛቱን ለመጠበቅ፣ እና መንፈሱ(መንፈሱ ቅድስ) ሁል ጊዜም ከእኛ ጋር ይሆን ዘንድ፣ ለአባታችን ለእግዚአብሔር ምስክር እንሆናለን።

    በአብ ቃል የተገቡልን ስጦታዎች በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያድን እና የሚያጠነክር ኃይል ይመጣሉ፡፡፡ ለምሳሌ, ፕሬዝዳንት ራስል ኤም.ኔልሰን እልዳስተማሩት, ኢየሱስ ክርስቶስ የደስታ ሁሉ ምንጭ ነው፡፡ደስታና መንፈሳዊ ደህንነት Liahona, ህዳር 2016, 82). እናም አትኩሮታችንን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ካጣበቅን በማንም አይነት ሁኔታዎች ውስጥ ብንሆን ደስታን ወደ ህይወታችን ያመጣልናል፡፡

  30. ፕሬዝዳንት እዝራ ተፍት ቤንሰን የዚህን ለውጥ ጽእኖ በአዕምሯዊ አስተያየት በዚህ መልኩ ተናግረዋል, መታዘዠ ወደ ብስጭትና ጥያቄ ሲያመራ በዛሰአት እግዚሐብሄር በሀይል ይሞሏናል ” (, “Oበዶናል ኤል ስትአልኒን መታዘዠ —የሂወት ትልቊ ፈተና,”,” Ensign, , ግንቦት 1998, 82).

  31. ዮሐንስ 16፥32።

  32. ስለ አብ ስለ ልጁ ለእኛ መጨነቅ፤ ስለእኛ ፍላጎት፤ ፍቅር፤በህይወታችን ተሳትፎ ለተጨማሪ መረጃ፤ ጀፍሪ አር ሆላንድ, “The Grandeur of God,” Liahona, ኃዳር. 2003, 70–73; ሄነሪ ቢ አይሪንግ, “Walk with Me,” Liahona,2017, 82–85. ይህንም ተመልከቱየማቲዎስ ወንጌል 18:2028:20ትምህርትና ቃልኪዳን6:3229:538;761;3684;88

  33. ሮሜ 8፤35-39 1 ቆሮንቶስ 13፤1-8 1 ቆሮንቶስ 13፤1-8ተመልከቱ።

  34. ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 50፥27። አስታውሱ፤ ጌታ ለእነዚያ ለተቀቡት ሁሉ ይስጣል እና ይህን ቃልኪዳኑንን ተፈፃሚ እንዲሆን ይልካል እና ይገደባዋልም፤ የተመርጠ የስራ ምድብ ይሰጠዋል፡፡

    ምንም እንኳን እርሱ ታናሽ እና የሁሉ አገልጋይ ቢሆንም፣ በእግዚአብሔር የተሾመ እና የተላከ፣ እርሱ ታላቅ ይሆን ዘንድ ተመርጧል።

    በመሆኑም፣ እርሱ የሁሉም ነገሮች ባለቤት ነው፤ በሰማይ እናም በምድር በልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ አብ ፈቃድ የተላኩ ነገሮች ሁሉ፣ ህይወት እና ብርሀን፣ መንፈስ እና ሀይል፣ ለእርሱ ተገዢ ናቸውና።

    ነገር ግን ከሁሉም ኃጢአት የጸዳ እና የነጻ ካልሆነ በስተቀር ማንም ሰው የሁሉም ነገሮች ባለቤት ሊሆን አይችልም።

    እና ከሁሉም ኃጢአቶች ከጸዳችሁ እና ከነጻችሁ፤ የምትሹትን ሁሉ በኢየሱስ ስም ትጠይቃላችሁ እናም ይህም ይከናወናል።(ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 50፥26–29)

  35. 1ኛ ሳሙኤል16:7 1 ቆሮንቶስ 2፤14 ተተመልከቱ.። ኢየሱስ እንዳየው እንድናይ እንባረካለን ለሚለው ምሳሌ፤ ፕሬዝዳንት ሄነሪ ቢ.አይሪንግ ወንጀል ለፈፀመ ወጣት፤ ኢጲስ ቆጶስ ሆነው ያሳለፉትን ተሞክሮ ተመልከቱ፡፡ ጌታ ለዛን ጊዜው ኢጲስ ቆጶስ አይሪንግ ‹‹እኔ እንደማየው እንድታየው አደርግሀለሁ›› አለው፡፡ ግንቦት 2017, 84). ከኔጋር ተራመድ

  36. በባውንትፉል ቤተመቅስ አዳኛችን ለህዝቡ ይህን ቃልኪዳን እና ኃላፊነት ሰጣቸው፡፡ ብርሃኑ እና ምሳሌው በእነሱ እንዲኖር አዘዛቸው፤ በህይወታቸው እናም ሌሎችን ወደእርሱ እንዲ መጡ ስንጋብዙ እርሱን እንደ አለም ብርሃን ከፍ አርገው እንዲይዙ፡፡ በመኖር፤ እና በመጋበዝ፤ ሌሎች እርሱን ይሰማቸዋል እና እርሱን እንደ በጌታ አገልጋዮች ውስጥ ያዩታል 3 ኔፊ 18፥24–25፣ ይመልከቱ።

  37. ራስል ኤም. ኔልሰን፣የክነስልጣን ሀይል ዋጋLiahona፣ ግንቦት 2016 (እ.አ.አ)፣ 68።ይመልከቱ።

  38. ትምህርት እና ቃል ኪዳን 84፥88 ተመልከቱ።

አትም