ትምህርት እና ቃልኪዳኖች፣ በመጨረሻው ቀናት የእግዚአብሔርን መንግስት በምድር ላይ ለማቋቋም እና ለማስተዳደር መለኮታዊ ራእዮች እና የተነሳሱ ምሪት የተሰጡ አዋጆች ስብስብ ነው። ምንም እንኳን አብዛኞቹ ክፍሎች የኋለኛው ቀን ቅዱሳን የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አባላትን የሚመለከቱ ቢሆኑም፣ መልእክቶቹ፣ ማስጠንቀቂያዎቹ፣ እና ማበረታቻዎቹ ለሰው ዘር በሙሉ ጥቅም ናቸው፤ እንዲሁም በሁሉም ቦታ ላሉት ሰዎች ሁሉ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስን ድምጽ ለጊዜአዊ ጥቅማቸውና ለዘለአለማዊ ደህንነታቸው ሲናገራቸው እንዲሰሙ ግብዣን የያዙ ናቸው።