Scripture Stories
ዳንኤል እና የአንበሶች ጕድጓድ


“ዳንኤል እና የአንበሶች ጕድጓድ፣” የብሉይ ኪዳን ታሪኮች [2022 (እ.አ.አ)]

“ዳንኤል እና የአንበሶች ጕድጓድ፣” የብሉይ ኪዳን ታሪኮች

ዳንኤል 6

ዳንኤል እና የአንበሶች ጕድጓድ

የአንድ ሰው ለመጸለይ ያለው ድፍረት

ምስል
ዳንኤል ንጉሱን ሲያነጋግረው

ዳርዮስ የባቢሎን ገዢ ሆነ እርሱም ዳንኤልን ይወድ ነበር እናም በግዛቱ ሁሉ እርሱን መሪ ለማድረግ ፈለገ። የንጉሱ አንዳንድ ጥበበኛ ሰዎች ቀንተው ነበር።

ዳንኤል 6፥1–4

ምስል
ጥበበኛ ሰዎች እያሴሩ

ጥበበኛ ሰዎች ዳንኤል ወደ እግዚአብሔር እንደሚጸልይ ያውቁ ነበር፣ ስለዚህ ንጉሱ አዲስ ህግ እንዲያውጅ አታለሉት። ማንም ለእግዚአብሔር የሚጸልይ ሰው ወደ አንበሳ ጉድጓግ ይጣላል።

ዳንኤል 6፥5–9

ምስል
ዳንኤል ሲጸልይ

ዳንኤል ይህም ቢሆን ወደ እግዚአብሔር ለመጸለይ መረጠ። የንጉሱ ጥበበኛ ሰዎችም ዳንኤል ሲጸልይ አዩት እናም ዳንኤል ህጉን እንደጣሰ ለንጉሱ ነገሩት። ንጉሱ ጥበበኛ ሰዎቹ እንዳታለሉት ተገነዘበ። ዳንኤልን የሚያድንበት መንገድ ለማግኘት ሞከረ፣ ነገር ግን ንጉሱ የራሱን ህግ መከተል ነበረበት።

ዳንኤል 6፥10–15

ምስል
ዳንኤል በአንበሶች ጕድጓድ ውስጥ

ዳንኤልም በአንበሶች ጕድጓድ ተጣለ። ዳንኤል እንዲጠበቅ እየጾመ፣ ንጉሱ ለሊቱን በሙሉ ሳያንቀላፋ አደረ።

ዳንኤል 6፥16–18

ምስል
ንጉሱ ዳንኤልን በአንበሶች ጉድጓድ ውስጥ ሲመለከተው

በነጋውም ንጉሡ ማልዶ ተነሣ፥ ፈጥኖም ወደ አንበሶቹ ጕድጓድ ሄደ። ዳንኤል አሁንም በህይወት እንዳለ ለማየትም ጠራው። ዳንኤልም መለሰለት! እግዚአብሔር የአንበሶችን አፍ ለመዝጋት መልአክን እንደላከ ለንጉሱ ነገረው። አንበሶቹ እርሱን አልጎዱትም።

ዳንኤል 6፥19–23

ምስል
ንጉሱ ዳንኤልን ሲያቅፈው።

ንጉሱ ዳንኤል ደህና በመሆኑ ተደስቶ ነበር። ያታለሉትን እነዚያን ጥበበኛ ሰዎች ቀጣ፣ እናም ህጉንም ሰረዘ። መንግስቱንም ስለእግዚአብሔር ሀይል እና መልካምነት አስተማረ።

ዳንኤል 6፥23–27

አትም