Scripture Stories
ፋሲካ


“ፋሲካ፣” የብሉይ ኪዳን ታሪኮች [2022 (እ.አ.አ)]

“ፋሲካ፣” የብሉይ ኪዳን ታሪኮች

ዘጸአት 11–12; 14–15

ፋሲካ

በጌታ መጠበቅ

ምስል
ሙሴ ሲፀልይ

ፈርኦን እስራኤላውያን ነጻ እንዲሆኑ አልፈቀደም፣ ስለዚህም ጌታ አንድ የመጨረሻ መቅሰፍት እንደሚልክ ለሙሴ ነገረው። በግብፅ ምድር የእያንዳንዱ ቤተሰብ የበኩር ልጅ፣ የእንስሶቻቸው በኩር ሳይቀር ይሞታል።

ዘጸአት 11፥1፣ 4–10

ምስል
ሙሴ ከሰዎች ጋር እያወራ

እስራኤላውያን የእርሱን መመሪያዎች ከተከተሉ መቅሰፍቱ ከእነርሱ እንደሚያልፍ እና እንደማይጎዳቸው ጌታ ቃል ገባ።

ዘጸአት 12፥3፣ 13፣ 23

ምስል
አንድ ሰው የበር መቃን እየቀባ፣ ልጆች እየተመለከቱ

ጌታ እያንዳንዱ የእስራኤል ቤተሰብ እንከን የለሽ ወንድ ጠቦት መሥዋዕት በማድረግ የጠቦቱን ደም በቤታቸው በር ላይ እንዲቀቡ ነገራቸው።

ዘጸአት 12፥4–7

ምስል
ቤተሰብ እራት እየበሉ

ጠቦቱን እንዲያበስሉ እና በፍጥነት እንዲበሉ ጌታ ለእስራኤላውያን ነገራቸው። በሚመገቡ ጊዜ፣ ልብሳቸውን ለብሰው እና ቤቶቻቸውን ጥለው ለመሄድ ይዘጋጁ። ጌታም እነዚህን ነገሮች እስራኤላውያን ካደረጉ፣ የበኩር ልጆቻቸው ከመቅሰፍቱ ይድናሉ አለ።

ዘጸአት 12፥8–11

ምስል
የፈርዖን ወንድ ልጅ ሞቶ

ጌታ እንዳስጠነቀቀው፣ መቅሰፍቱ መጣ። የፈርዖን የመጀመሪያ ወንድ ልጅን ጨምሮ በግብጽ ሁሉም የበኩር ልጆች ሞቱ። ነገር ግን መቅሰፍቱ በበሩ መቃን ላይ የጠቦት ደም ያለበትን እያንዳንዱን ቤት አለፈ። ለጌታ ታዛዥ በመሆናቸው ምክንያት የእስራኤላውያን የበኩር ልጆች ዳኑ።

ዘጸአት 12፥12–13፣ 29–30

ምስል
ያዘነው ፈርኦን ሙሴንና አሮንን እንዲሄዱ ሲነግራቸው

ፈርዖን በዚህ መቅሰፍት የገዛ ልጁ መሞቱን ባየ ጊዜ፣ ሙሴንና አሮንን እስራኤላውያንን ሁሉ ይዘው ከግብፅ እንዲወጡ ነገራቸው።

ዘጸአት 12፥31–33

ምስል
የተናደደው ፈርዖን ሰራዊት እየላከ

እስራኤላዊያን ሄዱ ነገር ግን ፈርዖን ተናዶ ነበር። ሠራዊቱንና እና ሠረገሎቹን ሰብስቦ እስራኤላውያንን አሳደዳቸው።

ዘጸአት 12፥37–4114፥5–8

ምስል
ሰራዊት እስራኤላውያንን እያሳደዳቸው

እስራኤላውያን በቀይ ባህር ሰፈሩ። ብዙም ሳይቆይ ፈርዖንና ሠራዊቱ ደረሱባቸው። እስራኤላውያን ግብፃውያን ሲመጡ ባዩ ጊዜ ፈርተው ነበር። ሙሴ ግን ጌታ እንደሚጠብቃቸው ለእስራኤላውያን ነገራቸው።

ዘጸአት 14፥9–14

ምስል
ሙሴ በትር ሲያነሳ፣ ቀይ ባህር ሲከፈል

ግብፃውያን እየቀረቡ ሲሄዱ፣ ጌታ ሙሴን በትሩን ከፍ እንዲያደርግ ነገረው። ሙሴም እንደተባለው አደረገ፣ እናም ጌታ ባህሩን ከፈለው። እስራኤላውያን ባሕሩን በደረቅ መሬት ተሻገሩ። ከፈርዖንና ከሠራዊቱ ሸሹ።

ዘጸአት 14፥15–16፤ 21–22

ምስል
ቀይ ባህር በግብፅ ሰራዊት ላይ ሲመለስ

የግብጽ ሠራዊት እስራኤላውያንን አሳደዷቸው። እስራኤላውያን ሁሉ በባሕሩ ማዶ በደህና ሲደርሱ ጌታ ውሃው እንዲመለስ አደረገ። የግብጽ ሠራዊት በባህር ውስጥ ሰመጡ።

ዘጸአት 14፥23–30

ምስል
እስራኤላውያን እየዘፈኑ

እስራኤላውያን በስተመጨረሻ ነጻ ሆኑ። መዝሙሮችን ዘመሩ፣ ጨፈሩ እና ጌታን አመሰገኑ፡፡ ጌታ ህይወታቸውን ያተረፈበት እና ከግብፅ ያወጣቸው ጊዜ እንደመሆኑ ሁልጊዜ ፋሲካን ያስታውሳሉ።

ዘጸአት 14፥3115፥1–22

አትም