Scripture Stories
የዮሴፍ በመንፈስ የተነሳሱ ህልሞች


“የዮሴፍ በመንፈስ የተነሳሱ ህልሞች፣” የብሉይ ኪዳን ታሪኮች [2022 (እ.አ.አ)]

“የዮሴፍ በመንፈስ የተነሳሱ ህልሞች፣” የብሉይ ኪዳን ታሪኮች

ዘፍጥረት 30፤ 37

የዮሴፍ በመንፈስ የተነሳሱ ህልሞች

እርስ በእርስ ለመዋደድ የሚደረግ የቤተሰብ ትግል

ምስል
ያዕቆብ እና የእርሱን ቀሚስ የተጎናጸፈው ዮሴፍ

ራሔል እና ያዕቆብ ወንድ ልጅ ለመውለድ ለብዙ ዓመታት ሲጸልዩ ነበር። ዮሴፍ በተወለደ ጊዜ ጌታ ጸሎታቸውን መለሰ። ዮሴፍ የያዕቆብ ተወዳጅ ልጅ ነበር እናም ለዮሴፍ ልዩ ቀሚስ ሰጠው። የያዕቆብ 10 ታላቅ ወንድ ልጆችም ቀኑ።

ዘፍጥረት 30፥22–2437፥1–4

ምስል
ዮሴፍ ስለእህል ህልምን እያብራራ

ዮሴፍ ወደ 17 ዓመት ገደማ ሲሆነው ከወንድሞቹ ጋር በሜዳ ላይ እህል እየሰበሰበ በመንፈስ አነሳሽነት ህልም አየ። የዮሴፍ እህል ጥቅል ከፍ ብሎ ቆመ። የወንድሞቹ እህል ጥቅሎች ግን ለዮሴፍ ጥቅል ሰገዱ። ዮሴፍ ስለህልሙ ለወንድሞቹ ሲነግራቸው ተቆጡ።

ዘፍጥረት 37፤ 2፣ 5–8

ምስል
ዮሴፍ ስለከዋክብት ህልም እያብራራ

ከጊዜ በኋላ ዮሴፍ በመንፈስ አነሳሽነት ሌላ ህልም አየ። በዚህ ህልም ፀሀይ፣ ጨረቃ እና 11 ከዋክብቶች ለእርሱ ሰገዱለት። ዮሴፍ ስለህልሙ ለቤተሰቡ ነገራቸው። ይህ ህልም ዮሴፍ በቤተሰቡ ላይ እንደሚመራ አይነት መሰለ። የዮሴፍ ወንድሞች በእርሱ ይበልጥ ተቆጡ። የእሱን ህልሞች አልወደዷቸውም።

ዘፍጥረት 37፥9–11

ምስል
ዮሴፍ ሰለወንድሞቹ ጤንነት ሲጠይቅ

አንድ ቀን የዮሴፍ ወንድሞች በጎቹን ሊመግቡ ከቤታቸው ርቀው ሄደው ነበር። ያዕቆብ ስለእነርሱ ጤንነት እንዲጠይቅ ዮሴፍን ላከው።

ዘፍጥረት 37፥12–19

ምስል
የዮሴፍ ወንድሞች

አንዳንድ የዮሴፍ ወንድሞች ሊገድሉት ፈለጉ። የዮሴፍን ቀሚስ ወሰዱና እርሱን ጉድጓድ ውስጥ ጣሉት።

ዘፍጥረት 37፥20–24

ምስል
ዮሴፍ በጉድጓድ ውስጥ

ዮሴፍ በጉድጓዱ ውስጥ ሳለ ወንድሞቹ ወደ ግብፅ የሚሄዱ መንገደኞችን ተመለከቱ። ወንድሞቹ ዮሴፍን ለመንገደኞቹ በ20 ብር ባሪያ አድርገው ለመሸጥ ወሰኑ።

ዘፍጥረት 37፥25–28

ምስል
በዮሴፍ ቀሚስ ላይ ደም

ከዚያም የዮሴፍ ወንድሞች የፍየል ደም በቀሚሱ ላይ አደረጉ። ወንድሞቹ ወደ አባታቸው ወደ ያዕቆብ ሄደው ቀሚሱን አሳዩት። ያዕቆብን ዋሹትና የዱር እንስሳት ዮሴፍን እንደገደሉ ነገሩት።

ዘፍጥረት 37፥31–33

ምስል
ያዕቆብ እያለቀሰ

ያዕቆብ ዮሴፍ የሞተ ስለመሰለው አለቀሰ።

ዘፍጥረት 37፥32–35

ምስል
ዮሴፍ እንደባርያ በግብፅ እየኖረ

ነገር ግን ዮሴፍ አሁንም በህይወት ነበር። ከአገሩ ርቆ በግብፅ ውስጥ እንደባሪያ ይኖር ነበር።

ዘፍጥረት 37፥36

አትም