Scripture Stories
ኢዮብ


“ኢዮብ፣” የብሉይ ኪዳን ታሪኮች [2021 (እ.አ.አ)]

“ኢዮብ፣” የብሉይ ኪዳን ታሪኮች

ኢዮብ 1–3፤ 19፤ 38–42

ኢዮብ

የጌታን ፍቅር ማመን

ምስል
ኢዮብ እና ቤተሰቡ እራት ሲበሉ

ኢዮብ ጌታን የሚወድና ትእዛዛቱን የሚያከብር መልካም ሰው ነበር። እርሱና ባለቤቱ 10 ልጆች ነበሯቸው እንዲሁም ብዙ የእንስሳት መንጋዎች እና ታላቅ ሀብት ነበረው።

ኢዮብ 1፥1–5

ምስል
ኢዮብ ማዕበልን እየተመለከተ

ጌታ የኢዮብ እምነት እንዲፈተን ፈቀደ። ኢዮብ ከባድ ነገሮች አጋጠሙት።

ኢዮብ 1፥6–12

ምስል
የኢዮብ ቤት እየነደደ

አንድ ቀን ብዙዎቹ የኢዮብ እንስሳት ተሰረቁ። በኋላም እሳት የኢዮብን መላ ንብረቶች አቃጥሎ አገልጋዮቹን ሁሉ እንዲሁም ሌሎች እንስሳቶቹን ሁሉ ገደለ። ከዚያም አውሎ ንፋስ የኢዮብን ልጅ ቤት አፈረሰ። ልጆቹም በውስጡ ነበሩ እናም ሁሉም ሞቱ። ኢዮብ እና ባለቤቱ ከጤንነታቸው በስተቀር ምንም አልነበራቸውም።

ኢዮብ 1፥13–19

ምስል
ኢዮብ እና ባለቤቱ ሲጸልዩ

ኢዮብ እና ባለቤቱ አዝነው ነበር። ልጆቻቸውንም ሳይቀር ሁሉንም አጥተው ነበር። ነገር ግን ኢዮብ አሁንም በጌታ ላይ እምነት ነበረው። ስለሆነው ነገር ጌታን አልወቀሰም።

ኢዮብ 1፥20–22

ምስል
የኢዮብ ባለቤት ታማሚውን ኢዮብ ስትመግብ

ከዚያም ኢዮብ በጣም ታመመ። ሰውነቱን የሚያም ቁስል ሸፈነው። ኢዮብ እና ባለቤቱ እነዚህ ሁሉ መጥፎ ነገሮች ለምን እየተከሰቱ እንደሆነ ለማወቅ ጓጉ።

ኢዮብ 2፥7–93፥1–11

ምስል
ኢየሱስ አጽናፈ ሰማዩን ለኢዮብ ሲያሳየው

ጌታ ኢዮብን አናገረው እናም ምድርን፣ ከዋክብትን፣ እና ህይወት ያላቸውን ነገሮች በሙሉ አሳየው። ጌታም ኢዮብን አስፈላጊ ትምህርት አስተማረው። ሁሉም ነገሮች የተፈጠሩት የሰማይ አባትን ልጆች ስለልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲማሩ እና እርሱን እንዲከተሉት ለመርዳት ነበር።

ኢዮብ 38–41

ምስል
ኢዮብ እና ቤተሰቡ

ኢዮብ ንስሀ ገባ በመጠራጠሩም ጌታን ይቅርታ ጠየቀ። በጌታ ለመታመን ቃል ገባ። ጌታ ኢዮብ እንደሚወደው አወቀ። ኢዮብን ፈወሰው እንዲሁም ተጨማሪ ልጆችን በመስጠትና አስቀድሞ ከነበረው በሁለት እጥፍ ሀብት በመስጠት ባረከው።

ኢዮብ 19፥25–2642

አትም