Scripture Stories
ነቢዩ ኢያሱ


“ነቢዩ ኢያሱ፣” የብሉይ ኪዳን ታሪኮች [2022 (እ.አ.አ)]

“ነቢዩ ኢያሱ፣” የብሉይ ኪዳን ታሪኮች

ዘዳግም 1031፤ 34ኢያሱ 13–610–1121፤ 24

ነቢዩ ኢያሱ

ወደቃል ኪዳኑ ምድር ከመገባቱ በፊት የመጨረሻው ፈተና

ምስል
ኢያሱ እየፀለየ

ነቢዩ ሙሴ ወደሰማይ ከተወሰደ በኋላ ጌታ ኢያሱን አዲሱ ነቢይ እንዲሆን ጠራው። እስራኤላውያን በዮርዳኖስ ወንዝ አቅራቢያ በሰፈሩበት ጊዜ፣ ጌታ ወደ ቃል ኪዳኑ ምድር የሚሄዱበት ጊዜ እንደደረሰ ተናገረ።

ዘዳግም 34፥1–9ኢያሱ 1፥1–4አልማ 45፥19

ምስል
በከነዓን ያሉ ክፉ ሰዎች

የቃል ኪዳኑ ምድር በከነዓን ነበር፤ ነገር ግን ክፉ ሰዎች እዚያ ይኖሩ ነበር። ጌታ ኢያሱን ብርታት እንዲኖረው እና እንዲጸና ነገረው። በጌታ እርዳታ እስራኤላውያን የከነዓንን ምድር ማሸነፍ ይችላሉ።

ኢያሱ 1፥1–9

ምስል
እስራኤላዊያን በዮርዳኖስ ወንዝ አጠገብ

ኢያሱ ሰራዊት ሰበሰበ። ጌታ የአሥርቱ ትእዛዛትን የድንጋይ ጽላቶች እና ሌሎች ቅዱሳት መጻሕፍትን እንዲሸከሙ ነገራቸው። ካህናቱ እነዚህን ቅዱስ ዕቃዎች የቃል ኪዳን ታቦት በተባለ ሳጥን ውስጥ ተሸከሙ። ከዚያም ሠራዊቱ የዮርዳኖስን ወንዝ ለመሻገር ተዘጋጀ። ወንዙ ጥልቅ ነበር እንዲሁም በፍጥነት ይሄድ ነበር።

ዘዳግም 10፥531፥25–26ኢያሱ 1፥10–113፥1–11

ምስል
ነቢዩ ኢያሱ

ጌታ ወንዙን እንዲሻገሩ እንደሚረዳቸው ኢያሱ ለእስራኤላውያን ቃል ገባላቸው።

ኢያሱ 3፥10–13

ምስል
ውሀ በእግር ዙሪያ ሲከፈል

ኢያሱ 12 ካህናት የቃል ኪዳኑን ታቦት እንዲሸከሙ እና ወደውሀው እንዲገቡ ጠየቃቸው። ካህናቱ ወንዙ ውስጥ እንደገቡ ውሀው ተከፈለ።

ኢያሱ 3፥12–17

ምስል
እስራኤላውያን በደረቅ ወንዝ ላይ የቃል ኪዳኑን ታቦት ተሸክመው፣ አንዳንዶቹ ድንጋይ እየሰበሰቡ

እስራኤላውያን ወንዙን በደረቅ መሬት ተሻገሩ። ኢያሱ ከደረቁ ወንዝ 12 ድንጋዮችን እንዲወስዱ እስራኤላውያንን ጠየቃቸው። በዚያን ቀን የነበረውን የጌታ ተአምር ለእስራኤላውያን ለማስታወስ ድንጋዮቹን ቆለላቸው።

ኢያሱ 3፥174፥1–24

ምስል
እስራኤላውያን በሰልፍ ወደ ከተማው ሲሄዱ

ኢያሱ የእስራኤላውያንን ሰራዊት ወደ ከነዓን ምድር መራ። ኢያሪኮ ወደምትባል ከተማ ደረሱ። ከተማዋ በጣም ጠንካራ ነበረች እንዲሁም ረዥም ግንቦች ነበሯት። ጌታ ኢያሪኮን እንዴት ማሸነፍ እንደሚቻል ለኢያሱ ነገረው። እስራኤላውያን ለስድስት ቀናት ያህል በየቀኑ ኢያሪኮን መዞር አለባቸው አለ። ኢያሱ ጌታን ታዘዘ።

ኢያሱ 5፥13–156፥1–5

ምስል
ካህናት የቃል ኪዳን ታቦቱን ተሸክመው፣ ሌሎች ቀንደ መለከቶችን እየነፉ

ኢያሱ የቃል ኪዳኑን ታቦት በእስራኤላውያን ፊት እንዲሸከሙ ለካህናቱ ነገራቸው። በየቀኑም ሠራዊቱ በኢያሪኮ ዙሪያ ዞረ እንዲሁም ሰባት ካህናት ቀንደ መለከታቸውን ነፉ። ሌሎቹ እስራኤላውያን ሁሉ ዝም አሉ።

ኢያሱ 6፥6–14

ምስል
እስራኤላውያን እየጮሁ፣ ግንብ እየፈረሰ

በሰባተኛው ቀን ሠራዊቱ በኢያሪኮ ዙሪያ ሰባት ጊዜ ዞሩ። ካህናቱ ቀንደ መለከታቸውን ሲነፉ ኢያሱ እስራኤላውያን እንዲጮኹ ነገራቸው። በድንገት የኢያሪኮ ግንብ ወደቀ፣ እናም የኢያሱ ሠራዊት ከተማይቱን ወሰደ።

ኢያሱ 6፥15–16፣ 20

ምስል
ኢያሱ በከተማ ውስጥ ለሰዎች ሲናገር

ጌታ ቃል እንደገባው እስራኤላውያንን ረዳቸው። የኢያሱ ሠራዊት የከነዓንን ምድር መውረሱን ቀጠለ፤ እናም እስራኤላውያን እዚያ መኖር ጀመሩ። ኢያሱም የጌታን ተአምራት እና ቃል ኪዳኖች አስታወሳቸው። እርሱም እስራኤላዊያን ጌታን ለማገልገል እንዲመርጡ ጠየቃቸው።

ኢያሱ 10፥4211፥2321፥43–4524፥15

አትም