Scripture Stories
ነቢዩ ሔኖክ


“ነቢዩ ሔኖክ፣” የብሉይ ኪዳን ታሪኮች [2022 (እ.አ.አ)]

“ነቢዩ ሔኖክ፣” የብሉይ ኪዳን ታሪኮች

ዘፍጥረት 5፤ ሙሴ 6–7

ነቢዩ ሔኖክ

በጌታ ያለ እምነት እንዴት አንድን ከተማ እንዳዳነ

ምስል
እግዚአብሔር ሔኖክን ሲያነጋግር

ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ህዝቡ ንስሐ እንዲገቡ እንዲነግራቸው ሔኖክን ጠየቀው። ሔኖክ ግን በደንብ መናገር እንደማይችል አሰበ። ህዝቡ አያደምጡኝም ብሎ ፈርቶ ነበር።

ዘፍጥረት 5፥22ሙሴ 6፥26–31

ምስል
ህዝቡ በሔኖክ ላይ ሲያፌዙ

አንዳንድ ሰዎች ሔኖክ ያስተማረውን ባይወዱትም፣ ጌታ ሔኖክን ለማጠናከር እና ለመጠበቅ ቃል ገባለት።

ሙሴ 6፥32–39

ምስል
ሔኖክ ህዝቡን ሲያስተምር

የጌታ ተስፋ ለሔኖክ ድፍረት ሰጠው። ሔኖክ ጌታን በመታዘዝ ህዝቡን በኃይል አስተማረ። ስለኢየሱስ ክርስቶስ፣ ንስሀ ስለመግባት፣ ስለጥምቀት፣ እና ስለመንፈስ ቅዱስ አስተማረ። አንዳንድ ሰዎች ሔኖክን አምነው ጌታን መከተል ፈለጉ።

ሙሴ 6፥47–68

ምስል
ሔኖክ ሴትን ሲያጠምቅ

ሔኖክ ለማጥመቅ ከእግዚአብሔር ስልጣን ነበረው። ሔኖክን ያመኑ ሰዎች በሙሉ ተጠመቁ እንዲሁም ወደ ጌታ ቀረቡ። እርስ በእርስ እንክብካቤ ይሰጣጡ ስለነበር ማንም ድሃ አልነበረም። በፍቅር እና በጽድቅ አብረው ስለኖሩ ፅዮን ተብለው ተጠሩ።

ሙሴ 7፥10–20

ምስል
የኢየሱስ ህይወት፣ ሞት፣ እና ትንሳኤ

አንድ ቀን ጌታ በምድር ላይ ወደፊት ስለሚሆነው ነገር ሁሉ ለሔኖክ በራእይ አሳየው። ሔኖክ የኢየሱስ ክርስቶስን ህይወት፣ ሞት እና ትንሳኤ አየ። በመጨረሻዎቹ ቀናት ወንጌል ዳግም እንደሚመለስ ሔኖክ ተረዳ። በተጨማሪም የኢየሱስን ዳግም ምጽዓት አየ።

ሙሴ 7፥21–67

ምስል
እግዚአብሔር ከፅዮን ህዝብ ጋር ሲነጋገር

በመጨረሻም፣ በፅዮን ከተማ የነበሩ ሰዎች ሁሉ ሔኖክን አምነው ንስሐ ገቡ። እርስ በእርስ እንክብካቤ ይሰጣጡ ስለነበር እና በሰላም ስለኖሩ፣ ጌታ ከእርሱ ጋር አብረው እንዲኖሩ ወሰዳቸው።

ዘፍጥረት 5፥24ሙሴ 7፥18፣ 21፣ 68–69

አትም