Scripture Stories
ኢኖስ


“ኢኖስ፣” የመፅሐፈ ሞርሞን ታሪኮች [2023 (እ.አ.አ)]

“ኢኖስ፣” የመፅሐፈ ሞርሞን ታሪኮች

ኢኖስ 1

ኢኖስ

ወደ ጌታ የቀረበ ታላቅ ጸሎት

ምስል
ኢኖስ በአደን ላይ

ያዕቆብ ሰሌዳዎችን ለልጁ ኢኖስ ሰጠ። ኢኖስ ያዕቆብ እንዳደረገው ጻፈባቸው። አንድ ቀን ኢኖስ በጫካ ውስጥ ለማደን ሄደ። አባቱ ስለጌታ ያስተማረውን አስታወሰ። ያዕቆብ ጌታን መከተል ደስታ እንደሚያመጣ ኢኖስን አስተምሮት ነበር።

ያዕቆብ 7፥27ኢኖስ 1፥2–3

ምስል
ኢኖስ በቀን እየፀለየ

ኢኖስ አባቱ የተናገረው ደስታ እንዲሰማው ፈለገ። ወደ ጌታ ለመጸለይ ወሰነ። ቀኑን በሙሉ እስከ ለሊት ድረስ ጸለየ።

ኢኖስ 1፥3–4

ምስል
ኢኖስ ወደ ላይ እየተመለከተ

ጌታ ለኢኖስ ኃጢያቱ ይቅር እንደተባለለት ነገረው። ኢኖስ በጣም ደስ አለው። ኢኖስ በኢየሱስ ክርስቶስ ባለው እምነት ተባረከ።

ኢኖስ 1፥3፣ 5–8

ምስል
ኢኖስ በሌሊት እየፀለየ

ኢኖስ ኔፋውያንም ይህ ደስታ እንዲሰማቸው ፈለገ። መፀለዩን ቀጠለ። ኔፋውያንም ተመሳሳይ ደስታ ሊሰማቸው ይችል ዘንድ ጌታን ጠየቀ።

ኢኖስ 1፥9

ምስል
ኢኖስ ደስተኛ መስሎ

ጌታ ኔፋውያን ትእዛዛቱን ከጠበቁ ከእነርሱ ጋር እንደሚሆን ለኢኖስ ነገረው። ኢኖስም ይህን በሰማ ጊዜ በጌታ ላይ ያለው እምነት ይበልጥ እየጠነከረ መጣ።

ኢኖስ 1፥10–11

ምስል
ኢኖስ በወርቅ ሰሌዳዎች ላይ እየፃፈ

ኢኖስ እንደገና ጸለየ። ጌታን ላማናውያንን እንዲባርክ እና በሰሌዳዎቹ ላይ ያሉትን ጽሁፍ እንዲጠብቅ ጠየቀ። ላማናውያን ሰሌዳዎቹን እንዲያነቡ እና በጌታ እንዲያምኑ ፈልጎ ነበር። ጌታ ላማናውያን ጽሁፎቹን አንድ ቀን እንደሚያነቡ ለኢኖስ ቃል ገባለት።

ኢኖስ 1፥11–17

አትም