Scripture Stories
ንጉስ ኖህ እና ንጉስ ሊምሂ


“ንጉስ ኖህ እና ንጉስ ሊምሂ፣” የመፅሐፈ ሞርሞን ታሪኮች [2023 (እ.አ.አ)]

ሞዛያ 19–22

ንጉስ ኖህ እና ንጉስ ሊምሂ

ከላማናውያን ማምለጥ

ምስል
ጌዴዎን ሰይፍ ይዞ ግንብ አጠገብ ቆሞ፣ ኖህ በግንቡ ላይ ሆኖ ወደ ላማናውያን ሰራዊት እያመለከተ

ንጉስ ኖህ የኔፋውያንን ቡድን ይገዛ ነበር። ብዙ መጥፎ ነገሮችን አድርጎ ስለነበር አንዳንድ ሰዎች በእሱ ይናደዱ ነበር። ጌዴዎን የሚባል ሰው ከኖህ ጋር በሰይፍ ተዋጋ። ኖህ ሮጦ አንድ ግንብ ላይ ወጣ። በግንቡ ላይ ሆኖ የላማናውያን ሰራዊት ሲመጣ አየ። ኖህ ለህዝቡ እንደፈራ ስላስመሰለ፣ ጌዴዎን በህይወት አተረፈው።

ሞዛያ 11፥1–219፥2–8

ምስል
ኖህ እየሸሸ እንዲሁም የኖህ ህዝቦች ፈርተው እንዳሉ

ኖህ እና ህዝቡ ሸሹ። ነገር ግን ላማናውያን አሳደዷቸው ከዚያም እነርሱን ማጥቃት ጀመሩ። ኖህ፣ ወንዶቹ ቤተሰቦቻቸውን ትተው ከእርሱ ጋር እንዲሄዱ ነገራቸው።

ሞዛያ 19፥9–11

ምስል
ሊምሂ፣ ጌዴዎን እና ሌሎች ኔፋውያን የላማናውያንን ሠራዊት ተጋፈጡ

አንዳንድ ወንዶች ከኖህ ጋር ሄዱ። ነገር ግን ብዙዎቹ ወንዶች ከቤተሰቦቻቸው ጋር መሆንን መረጡ። የኖህ ልጅ ሊምሂም መቆየትን መረጠ።

ሞዛያ 19፥12፣ 16–17

ምስል
ሴቶች በሊምሂ እና በሌሎቹ ኔፋውያን ፊት ቆመው

ብዙ ሴት ልጆች በሠራዊቱ ፊት በመቆም ላማናውያን ቤተሰቦቻቸውን እንዳይጎዱ ጠየቁ። ላማናውያን ሴት ልጆቹን ሰሙ እናም ኔፋውያን በህይወት እንዲኖሩ ፈቀዱላቸው። በምትኩ፣ ላማናውያን ኔፋውያንን በምርኮ ያዙ።

ሞዛያ 19፥13–15

ምስል
ኖህና ወንዶቹ አንዳቸው በሌላው ላይ ተናደዱ።

ሸሽተው የነበሩት ወንዶች ወደ ቤተሰቦቻቸው ለመመለስ ፈለጉ። ኖህ ሊያስቆማቸው በመሞከሩ ሰዎቹ ገደሉት። ከዚያም ወደ ቤተሰቦቻቸው ተመለሱ።

ሞዛያ 19፥18–22

ምስል
የኔፋውያን ወንዶች ለቤተሰቦቻቸው እና ለጌዴዎን ሰላምታ እያቀረቡ

ወንዶቹ ቤተሰቦቻቸው ደህና በመሆናቸው በጣም ተደሰቱ። ኖህ ላይ የከሰተውን ለጌዴዎን ነገሩት።

ሞዛያ 19፥22–24

ምስል
ሊምሂ ለላማናውያን ምግብ እና እንስሳትን እየሰጠ

ህዝቡ ሊምሂ አዲሱ ንጉሳቸው እንዲሆን መረጡት። ሊምሂ፣ እነርሱ ካላቸው ነገር ግማሹን ለላማናውያን እንደሚከፍሉ ለላማናውያን ንጉሥ ቃል ገባ። በምላሹም፣ የላማናውያን ንጉስ የሊምሂን ህዝብ እንደማይጎዳ ቃል ገባ።

ሞዛያ 19፥25–27

ምስል
ሊምሂ እና ሚስቱ አዝነው፣ ብዙ ኔፋውያን ተጎድተው

ለብዙ ዓመታት በሰላም ኖሩ። ከዚያም ላማናውያን የሊምሂን ሰዎች መጉዳት ጀመሩ። ህዝቡ ዳግም ነፃ መሆን ፈለገ። ላማናውያንን ለመዋጋት ሞከሩ፣ ነገር ግን ተሸነፉ። ህዝቡ ለእርዳታ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ።

ሞዛያ 19፥2921፥1–15

ምስል
ሊምሂ እና አሞን እያወሩ

አንድ ቀን፣ አሞን የሚባል ኔፋውያን ሊምሂን እና ህዝቡን ጎበኘ። አሞን ዛራሔምላ ከምትባል አገር መጣ። ሊምሂ አሞንን በማየቱ ተደሰተ።

ሞዛያ 21፥22–24

ምስል
ጌዴዎን፣ ሊምሂ፣ አሞን እና ሌሎች ኔፋውያን እየተነጋገሩ

አሞን የሊምሂን ህዝቦች ወደ ዛራሔምላ ሊመራ ይችላል፣ ነገር ግን መጀመሪያ ከላማናውያን ማምለጥ ነበረባቸው። ጌዴዎን እቅድ ነበረው።

ሞዛያ 21፥3622፥1–9፣ 11

ምስል
የላማናውያን ጠባቂዎች ተኝተው እያለ፣ ኔፋውያን ከተማዋን ለቀው እየወጡ

በሌሊት፣ የላማናውያን ጠባቂዎች እንዲተኙ ለማድረግ ጌዴዎን ተጨማሪ ወይን ሰጣቸው። ጠባቂዎቹ ተኝተው ሳለ፣ ሊምሂ እና ሁሉም ህዝቦቹ ከከተማው አመለጡ።

ሞዛያ 22፥7፣ 10–12

ምስል
ንጉስ ሞዛያ እና ህዝቡ ሊምሂን እና ህዝቡን ተቀበሉ

ወደ ዛራሔምላ በመሄድ ከኔፋውያን ጋር ተቀላቀሉ። ሊምሂ እና ህዝቡ ስለ እግዚአብሔር የበለጠ ተማሩ። እግዚአብሔርን ለማገልገል እና ትእዛዙን ለመጠበቅ ቃል ኪዳን ወይም ልዩ ኪዳን ገቡ። ተጠምቀው የእግዚአብሔር ቤተክርስቲያን አካል ሆኑ። እግዚአብሔር ከላማናውያን እንዲያመልጡ እንደረዳቸው አስታወሱ።

ሞዛያ 21፥32–3522፥13–1425፥16–18

አትም