Scripture Stories
አሞን


“አሞን፣” የመፅሐፈ ሞርሞን ታሪኮች [2023 (እ.አ.አ)]

አልማ 17–18

አሞን

ትሁት አገልጋይ

ምስል
አሞን እና ወንድሞቹ እየተሰናበቱ

አሞን እና ወንድሞቹ ላማናውያንን ስለ ጌታ ሊያስተምሯቸው ፈለጉ። ላማናውያን ይኖሩበት ወደነበረ ምድር ሄዱ። በመንገዳቸውም ጌታ እንዲረዳቸው ጾሙ እንዲሁም ጸለዩ። ጌታም አፅናናቸው። ታጋሽ እና ጥሩ ምሳሌ እንዲሆኑ ነገራቸው። እያንዳንዳቸውም ወደ ተለያዩ ቦታዎች በመሄድ ማስተማር ጀመሩ።

ሞዛያ 28፥1–2አልማ 17፥6–13

ምስል
አሞን በንጉሡ እና በንግሥቲቱ ፊት ተንበርክኮ

አሞን እስማኤል ወደሚባል ቦታ ሄደ። በዚያ ያሉት ሰዎች አስረውት ወደ ንጉሥ ላሞኒ ወሰዱት። አሞን ከላማናውያን ጋር መኖር እንደሚፈልግ ለላሞኒ ነገረው። ላሞኒ አሞንን ስለወደደው ነጻ አወጣው። አሞን ከሴት ልጆቹ መካከል አንዷን እንዲያገባ ፈለገ፣ ነገር ግን አሞን የላሞኒ አገልጋይ መሆንን መረጠ።

አልማ 17፥20–25

ምስል
አሞን በትከሻው ላይ አሻግሮ በጎችን እየተመለከተ

ላሞኒ፣ አሞን እንስሳቱን እንዲንከባከብ ነገረው። አንድ ቀን፣ አሞን እና አንዳንድ አገልጋዮች ውሃ ለመቅዳት እንስሳቱን ይዘው ሄዱ። እንስሳቱ እየጠጡ ሳለ ዘራፊዎች መጥተው አባረሯቸው። ሌሎቹ አገልጋዮች የላሞኒ እንስሳት በመጥፋታቸው እንዳይቀጡ ፈሩ።

አልማ 17፥25–28አልማ 18፥7

ምስል
አሞን

አሞን ይህ የጌታን ኃይል ለማሳየት አጋጣሚ እንደሆነ አወቀ። ሌሎቹ አገልጋዮች እንዳይጨነቁ ነገራቸው እንዲሁም የጠፉትን እንስሳት እንዲያገኙ ረዳቸው።

አልማ 17፥29–32

ምስል
አሞን የቆዳ ወንጭፍ በዘራፊዎች ላይ እያነጣጠረ

ዘራፊዎቹ እንደገና እንስሳቱን ለመበታተን ተመለሱ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ፣ አሞን ሌሎች አገልጋዮች እንዲቆዩ እና እንስሳቱ እንዳይጠፉ እንዲጠብቁ ነገራቸው።

አልማ 17፥33

ምስል
አሞን በዘራፊዎች ፊት ቆሞ

አሞን ዘራፊዎቹ በጎቹን እንዳይበትኑ ለማስቆም ሄደ። ዘራፊዎቹ አሞንን አልፈሩትም። ከእርሱ በላይ ጠንካሮች የሆኑ መስሏቸው ነበር። ነገር ግን ጌታ አሞንን እየረዳ እንደነበረ አላወቁም።

አልማ 17፥34–35

ምስል
አሞን በዘራፊዎች ላይ በወንጭፍ ድንጋይ እየወረወረ

አሞን በዘራፊዎቹ ላይ በወንጭፉ ድንጋይ ወረወረ። አንዳንዶቹ ሞቱ። ይህ ሌሎቹን ዘራፊዎች አስቆጣ፣ ስለሆነም አሞንን ሊገድሉት ፈለጉ። አሞንን በድንጋያቸው መምታት ባለመቻላቸው ተደነቁ። ይህን ያህል ኃያል ይሆናል ብለው አልጠበቁም ነበር።

አልማ 17፥36

ምስል
ዘራፊዎች ዱላ ሲያነሱበት አሞን ሰይፉን እየዘረጋ

ዘራፊዎቹ አሞንን በዱላቸው ሊመቱት ሞከሩ። ነገር ግን በሞከሩ ቁጥር አሞን እንዳይዋጉ እጆቻቸውን በሰይፍ ይቆርጥ ነበር። ብዙም ሳይቆይ ውጊያውን ለመቀጠል በጣም ፈሩና ሮጠው ሸሹ።

አልማ 17፥37–39

ምስል
ሁለት አገልጋዮች የሆነውን ነገር ለንጉሥ ላሞኒ እያስረዱ

አገልጋዮቹ አሞን እንስሳትን እንዴት እንዳዳናቸው ለላሞኒ ነገሩት። ላሞኒ ተገረመ። አሞን ታላቅ ኃይል ያለው እና ሁሉንም ነገር የሚያውቀውን ታላቁ መንፈስ እንደሆነ አሰበ።

አልማ 18፥1–5፣ 18

ምስል
ንጉስ ላሞኒ የተጨነቀ መስሎ

ላሞኒ ከአሞን ጋር መነጋገር ፈልጎ ነበር፣ ነገር ግን ተጨንቆም ነበር።

አልማ 18፥8–11

ምስል
አሞን በንጉሥ ላሞኒ ፊት ተንበርክኮ

አሞን ላሞኒን ለማየት ሄደ፣ ነገር ግን ላሞኒ ምን ማለት እንዳለበት አላወቀም ነበር። ጌታ፣ አሞን የላሞኒን ሃሳብ እንዲያውቅ ረዳው። አሞን ታላቁ መንፈስ እሱ እንዳልሆነ ተናገረ። ታላቁ መንፈስ እግዚአብሔር እንደሆነ ለላሞኒ ነገረው። ላሞኒ ስለ እግዚአብሔር የበለጠ ለማወቅ ፈለገ።

አልማ 18፥12–28

ምስል
አሞን ከንጉሥ ላሞኒ ጋር እየተነጋገረ

አሞን እግዚአብሔር አለምን እና በውስጡ ያሉትን ሁሉ እንደፈጠረ ተናገረ። ከዚያም አሞን እግዚአብሔር የማዳን እቅድ እንዳለው ለላሞኒ ነገረው። እንደዚያ እቅድ አካል፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ይመጣል። ላሞኒም አሞን ያለውን አመነ። ላሞኒ እግዚአብሔር ለእሱ እና ለህዝቡ ምህረት እንዲያደርግ በጸሎት ጠየቀ።

አልማ 18፥24–36፣ 39–42

አትም