Scripture Stories
ነቢዩ ኤተር


“ነቢዩ ኤተር፣” የመፅሐፈ ሞርሞን ታሪኮች [2023 (እ.አ.አ)]

ኤተር 612–15

ነቢዩ ኤተር

ጌታ ለአንድ ህዝብ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

ምስል
ደስተኛ ሰዎች በከተማ ገበያ ውስጥ

ጌታ የያሬድን ወንድም እና ቤተሰቡን ወደ ቃል ኪዳኗ ምድር አመጣ። ትሑት እና የእግዚአብሔርን ትእዛዛት የሚጠብቁ ነበሩ። ቡድናቸው ለብዙ ዓመታት አደገ እናም የሚመራቸውን ንጉስ ፈለጉ። የያሬድ ወንድም የንጉሥ መኖር ወደ ችግር ሊመራቸው እንደሚችል አስጠነቀቃቸው፣ ነገር ግን ንጉሥ እንዲመርጡ ፈቀደላቸው።

ኤተር 6፥5፣ 12–18፣ 22–24፣ 27

ምስል
ያሬዳውያን በቁጣ ኤተር ላይ ጣታቸውን ቀስረው

ለብዙ መቶ ዓመታት፣ ያሬዳውያን በቃል ኪዳኗ ምድር ውስጥ ኖሩ። አንዳንድ ጊዜ ንጉሦቻቸው መልካም ነገር እንዲያደርጉ ሲመሯቸው ሌላ ጊዜ ግን አላደረጉም። የእግዚአብሔር ነቢያት ህዝቡ ንስሐ እንዲገባ ያስጠነቅቁ ነበር። የእግዚአብሔርን ትእዛዛት ሲሰሙ እና ሲጠብቁ፣ እርሱም ይባርካቸው ነበር። የመጨረሻው የያሬዳውያን ነቢይ ኤተር ይባል ነበር።

ኤተር 7፥23–279፥26–3010፥16–17፣ 2811፥1–8፣ 12–13፣ 20–2212፥2

ምስል
ኤተር ተቀምጦ እያስተማረ እና አንዳንድ ሰዎች ተቆጥተው

ህዝቡ እግዚአብሔርን እየታዘዘ አልነበረም። የጌታ መንፈስ ግን ከኤተር ጋር ነበር። ከጠዋት እስከ ማታ አስተማራቸው። በእግዚአብሔር እንዲያምኑ እና ንስሐ እንዲገቡ አለበለዚያ እንደሚጠፉ ተናገረ። እምነት ቢኖራቸው እንደገና ከእግዚአብሔር ጋር የመኖር ተስፋ እና መልካም ነገር ለማድረግ ጥንካሬ ይኖራቸው ነበር። ሰዎቹ አላመኑም።

ኤተር 11፥2212፥2–513፥2

ምስል
ኤተር በዋሻ ውስጥ ተቀምጦ እየጻፈ

ኤተር ሰዎቹ ያደርጉ የነበረውን ተመለከተ። ቀን ቀን ዋሻ ውስጥ እየተደበቀ ያየውን ይጽፍ ነበር። ህዝቡ ንስሃ አልገባም እንዲሁም እርስ በርስ መጣላት ጀምረው ነበረ።

ኤተር 13፥13–15

ምስል
ቆሪያንተመር ወደፊት እያየ

ኤተር፣ የያሬዳዊውያን ንጉስ ቆሪያንተመር ንጉስ ለመሆን የሚፈልጉ ብዙ ሰዎችን መዋጋት እንደነበረበት ተመለከተ። ቆሪያንተመር ራሱን ለመከላከል ሠራዊቱን ተጠቀመ።

ኤተር 12፥113፥15–19

ምስል
ኤተር ቆሪያንተመርን እያነጋገረ

አንድ ቀን፣ ቆሪያንተመር እና ህዝቡ ንስሃ እንዲገቡ እንዲያስጠነቅቅ ጌታ ለኤተር ነገረው። ያንን ካደረጉ፣ ጌታ ህዝቡን ይረዳል እንዲሁም ቆሪያንተመር መንግስቱን ይዞ እንዲቀጥል ይፈቅዳል። ይህ ካልሆነ፣ ህዝቡ እርስ በርሱ ይጠፋፋል። ቆሪያንተመር የጌታን ቃል እውነት መሆኑን ለማየት ረጅም ዕድሜ ይኖረዋል። ከዚያም እሱም ይሞታል።

ኤተር 13፥20–21

ምስል
ሺዝ እና ሠራዊቱ ከቆሪያንተመር ሠራዊት ጋር እየተዋጉ፣ ኤተር እየተመለከተ

ቆሪያንተመር እና ህዝቡ ንስሃ አልገቡም። ህዝቡ ኤተርን ለመግደል ሞከሩ፣ ነገር ግን ኤተር ወደ ዋሻው አመለጠ። ሺዝ የሚባል ሰው ከቆሪያንተመር ጋር ተዋጋ። ህዝቡ ከሺዝ ወይም ከቆሪያንተመር ሠራዊት አንዱን ለመቀላቀል መረጡ። ሁለቱ ሠራዊቶች ብዙ ጦርነቶችን አደረጉ። ብዙ ሰዎች ሞቱ።

ኤተር 13፥22–2514፥17–2015፥2

ምስል
የቆሪያንተመር ሠራዊት ከሺዝ ሠራዊት ጋር እየተዋጋ፣ ቆሪያንተመር፣ ደብዳቤ እየጻፈ

ቆሪያንተመር ኤተር የተናገረውን አስታወሰ። ብዙ የእርሱ ህዝቦች በመሞታቸው አዘነ። ይህ እንደሚሆን ሁሉም ነቢያት አስጠንቅቀው የነበረውን አስታወሰ። ንስሃ መግባት ጀመረ እንዲሁም ለሺዝ ደብዳቤ ላከ። ህዝቡ መዳን ከቻለ መንግስቱን አሳልፎ እንደሚሰጥ ተናገረ። ነገር ግን ሺዝ ለመዋጋት ፈለገ።

ኤተር 15፥1-5

ምስል
ወንዶች፣ ሴቶች እና ህጻናት እንደ ወታደር እየዘመቱ፣ ኤተር ደግሞ እየተመለከተ

የቆሪያንተመር ህዝብ ተናድደው ነበር፣ እናም ለመዋጋት ፈለጉ። የሺዝ ህዝብም ተናድደው ነበር፣ እናም መዋጋት ፈለጉ። ማንም ንስሐ መግባት አልፈለገም። ኤተር እያንዳንዱ ሰው ወደ ጦርነት እንደሄደ ተመለከተ። ተጨማሪ ብዙ ሰዎች ሞቱ።

ኤተር 15፥6፣ 12–17

ምስል
ቆሪያንተመር ጦር ይዞ ዝናብ ላይ ተንበርክኮ

ቆሪያንተመር ጦርነቱን ለማቆም ፈለገ። እርሱም መንግስቱን እንዲወስድ እንዲሁም ህዝቡን እንዳይጎዳ ሺዝን ጠየቀ። ነገር ግን ሁሉም ሰው ተናድዶ ነበር። የጌታ መንፈስ አልነበራቸውም። ኤተር ከያሬዳዊያን መካከል በህይወት የተረፈው ቆሪያንተመር ብቻ እስኪሆን ድረስ ሁሉም ሲዋጋ አየ። ከዚያም ቆሪያንተመር ራሱን ስቶ ወደቀ።

ኤተር 15፥18–30፣ 32

ምስል
ኤተር በኮረብታ ላይ ባለው መሠዊያ ላይ ተንበርክኮ ወደ እግዚአብሔር እየጸለየ፣ መዝገቦች በአቅራቢያው ባለ ዋሻ ውስጥ ተከማችተው

ኤተር፣ ጌታ የተናገረው ሁሉ እውነት እንደሆነ አየ። ኤተር የተከሰተውን ነገር ጽፎ ጨረሰ። ከዚያም እሱ ካለፈ በኋላ ሰዎች ጽሑፎቹን ማግኘት እንዲችሉ አደረገ። ኤተር እግዚአብሔርን ያምን ነበር እንዲሁም አንድ ቀን ከእርሱ ጋር ለመሆን ይጓጓ ነበር።

ኤተር 15፥33–34

አትም