Scripture Stories
ሊያሆና እና የተሰበረው ቀስት


“ሊያሆና እና የተሰበረው ቀስት፣” የመፅሐፈ ሞርሞን ታሪኮች [2023 (እ.አ.አ)]

1 ኔፊ 16

ሊያሆና እና የተሰበረው ቀስት

የጌታን እርዳታ መፈለግ

ምስል
በሚነድ እሳት ዙሪያ የተቀመጡ ቤተሰቦች

የሌሂ እና የእስማኤል ቤተሰቦች ለብዙ አመታት በምድረበዳ ተጉዘዋል። ጌታ በመልካሙ የምድር ክፍል መራቸው። በመንገድ ላይ ማደን እና ምግብ መሰብሰብ ነበረባቸው። ጉዞው ከባድ ነበር።

1 ኔፊ 16፥1417፥14

ምስል
ሌሂ የፀሀይ መውጣትን ሲመለከት

ቤተሰቦቹ ትእዛዛቱን ከጠበቁ ወደ ጥሩ ምድር እንደሚመራቸው ጌታ ቃል ገባላቸው። ምድሪቱን እንዴት እንደሚያገኙ አያውቁም ነበር፣ ነገር ግን እርሱ ይመራቸዋል።

1 ኔፊ 2፥2010፥1317፣13–14

ምስል
ሌሂ ሊያሆናውን ይዞ

በአንድ ማለዳ ሌሂ ከድንኳኑ ውጭ የነሐስ ኳስ በማግኘቱ ተገረመ። ኳሱ ሊያሆና ይባል ነበር። በሊያሆና ውስጥ ያለው አንድ ቀስት ቡድኑ ሊጓዝበት የሚገባውን መንገድ ይጠቁም ነበር። አንዳንድ ጊዜ የጌታ መልእክቶች በሊያሆና ላይ ተፅፈው ያገኙ ነበር። በዚህ መንገድ ነበር ጌታ የመራቸው።

1 ኔፊ16፥10፣ 16፣ 26–29አልማ 37፥38

ምስል
ኔፊ የተሰበረ ቀስት ይዞ እና ላማን እና ልሙኤል ሲያጉረመርሙ

አንድ ቀን ኔፊ እያደነ ሳለ፣ የብረት ቀስቱ ተሰበረ። ቤተሰቦቹ ያለሱ ምግብ ማግኘት አልቻሉም። የኔፊ ወንድሞች በእርሱ እና በጌታ ተቆጡ።

1 ኔፊ 16፥18–21

ምስል
ኔፊ የተሰበረ ቀስት ይዞ እና ሌሂ እየተቀጣ

ሁሉም በጣም ደክመው እና ተርበው ነበር። አንዳንዶቹ አዝነው እና አጉረምርመው ነበር። እንራባለን ብለው ፈርተው ነበር። ሌሂም እንኳን በጌታ ላይ አጉረመረመ።

1 ኔፊ 16፥19–22፣ 35

ምስል
ኔፊ መዶሻ እና መሮ ይዞ

ኔፊ ከእንጨት የተሠራ አዲስ ቀስት እና ፍላጻ ሠራ። ጌታ ምግብ እንዲያገኝ እንደሚረዳው እምነት ነበረው።

1 ኔፊ 16፥23

ምስል
ሌሂ እና ኔፊ ሊያሆናን እየተመለከቱ

ኔፊ ለማደን የት መሄድ እንዳለበት ሌሂን ጠየቀው። ሌሂ ስላጉረመረመ ተጸጸተ። ንስሀ ገባ እንዲሁም ጌታ እንዲረዳው ጠየቀ። ጌታም ሌሂ ሊያሆናውን እንዲመለከት ነገረው። መልእክት ተጽፎበት ነበር። ሊያሆናው የሚሰራው በጌታ ላይ እምነት ሲኖራቸው እና ትእዛዛቱን ሲያከብሩ ብቻ እንደሆነ ቤተሰቦቹ ተረዱ።

1 ኔፊ 16፥23–29

ምስል
የሌሂ ቤተሰብ ኔፊ ያደነውን አውሬ ተሸክሞ ሲመጣ ሲመለከቱ

እነርሱን በጉዞአቸው ለመርዳት ጌታ በሊያሆና ላይ ያለውን መልእክት አንዳንድ ጊዜ ይቀይራል። ሊያሆናው ኔፊ የት ማደን እንዳለብት ለማወቅ ረዳው። የሚመገቡት ምግብ አመጣ፣ እናም ሁሉም ደስተኞች ነበሩ። ንስሀ ገቡ እንዲሁም ጌታን አመሰገኑ።

1 ኔፊ 16፥23–32

አትም