Scripture Stories
ሻምበል ሞሮኒ እና ዛራሔምና


“ሻምበል ሞሮኒ እና ዛራሔምና፣” የመፅሐፈ ሞርሞን ታሪኮች [2023 (እ.አ.አ)]

አልማ 43–44

ሻምበል ሞሮኒ እና ዛራሔምና

ጦርነት እና በሰላም ለመኖር ቃል ኪዳን

ምስል
ዛራሔምና ሠራዊቱን እየመራ

ዛራሔምና የላማናውያን ሠራዊት መሪ ነበር። በኔፋውያን ላይ መግዛት እና ህዝቡን እንዲያገለግሉ ለማድረግ ፈለገ። ዛራሔምና ሰራዊቱ ኔፋውያንን እንዲያጠቃ መራ።

አልማ 43፥3–8

ምስል
የኔፋውያን ሰራዊት የላማናውያንን ሰራዊት እየተመለከተ

ኔፋውያን ቤታቸውን፣ ቤተሰባቸውን እና ሃይማኖታቸውን ለመጠበቅ ፈለጉ። ላማናውያን የሚገዟቸው ከሆነ ጌታን ማምለክ እንደማይችሉ ያውቁ ነበር። ኔፋውያን ጠላቶቻቸውን ለመዋጋት መረጡ።

አልማ 43፥9–10፣ 14–15

ምስል
ሞሮኒ ከዳመና ፊት ሆኖ ወደፊት እየተመለከተ

የኔፋውያን ሠራዊት ሻምበል የሆነ ሞሮኒ የሚባል ሰው ነበር። ሞሮኒ ሠራዊቱ ለውጊያ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋገጠ።

አልማ 43፥16–17

ምስል
ሻምበል ሞሮኒ እና የኔፋውያን ወታደሮች ለመዋጋት ዝግጁ ሆነው

የሞሮኒ ወታደሮች መሳሪያ አመጡ፣ እንዲሁም ሞሮኒ እነሱን ለመጠበቅ ጠንካራ ጥሩር እና ጋሻ ሰጣቸው።

አልማ 43፥18–19

ምስል
ላማናውያን የኔፋውያንን ሠራዊት በፍርሃት እየተመለከቱ

ሞሮኒ ላማናውያንን ለመውጋት ሠራዊቱን ይዞ ሄደ። ነገር ግን ላማናውያን ኔፋውያን ጥሩር እና ጋሻ እንዳላቸው ባዩ ጊዜ ለመዋጋት ፈሩ። ላማናውያን ሥሥ ልብስ ብቻ ነበራቸው እንዲሁም የሚከላከላቸው ትጥቅ አልነበራቸውም።

አልማ 43፥19–21

ምስል
የላማናውያን ወታደሮች ጫካ ውስጥ እየሮጡ

ላማናውያን ሸሹ። ወደ ሌላ የኔፋውያን ምድር በድብቅ ለመግባት ሞከሩ። ሞሮኒ የት እንደሄዱ የማያውቅ መስሏቸው ነበር።

አልማ 43፥22

ምስል
የኔፋውያን ሰላዮች የላማናውያን ወታደሮች ሲሮጡ እየተመለከቱ

ነገር ግን ላማናውያን እንደሸሹ፣ ሞሮኒ እንዲከተሏቸው ሰላዮችን ላከ።

አልማ 43፥23

ምስል
የኔፋዊ ወታደር አልማን እያደመጠ

ከዚያም ሞሮኒ ለነቢዩ አልማ መልእክት ላከ። አልማ ላማናውያን ምን ለማድረግ እንዳሰቡ ጌታን እንዲጠይቅ ፈለገ። ጌታ፣ ላማናውያን ማንቲ የተባለ ደካማ ምድርን ለማጥቃት እንዳቀዱ ለአልማ ነገረው። ሞሮኒ አልማን አዳመጠ። ከላማናውያን ጋር ለመዋጋት ሠራዊቱን መራ።

አልማ 43፥23–33

ምስል
የላማናውያን እና የኔፋውያን ወታደሮች አንዳቸው ሌላውን እየተዋጉ

ሠራዊቱ ተዋጋ። ላማናውያን በጣም ጠንካሮች እና ቁጡዎች ነበሩ። ኔፋውያን ላማናውያንን ፈርተው ስለነበር ሊሸሹ ፈለጉ። ነገር ግን ሞሮኒ ቤተሰቦቻቸውን እና እምነታቸውን አስታወሳቸው፣ ስለዚህ መዋጋታቸውን ቀጠሉ።

አልማ 43፥34–37፣ 43–48

ምስል
ሞሮኒ ጦርነቱን ለማቆም እጁን ዘርግቶ

ኔፋውያን ለእርዳታ ወደ ጌታ ጸለዩ። ጌታ ጸሎታቸውን ሰማ፣ ታላቅም ኃይል ሰጣቸው። አሁን ላማናውያን ፈሩ። እነርሱም ወጥመድ ውስጥ ገቡ፣ ማምለጥም አልቻሉም። ሞሮኒ ላማናውያን እንደፈሩ ባየ ጊዜ፣ ወታደሮቹ ውጊያ እንዲያቆሙ ነገራቸው። ሞሮኒ ላማናውያንን መግደል አልፈለገም።

አልማ 43፥49–5344፥1–2

ምስል
ሞሮኒ ለላማናውያን እየተናገረ

ሞሮኒ፣ ላማናውያን ኔፋውያንን ዳግም ላለመዋጋት ቃል የሚገቡ ከሆነ መሄድ እንደሚችሉ ለዛራሔምና ነገረው። ዜራሔምና ተቆጣ፣ ውጊያውን ለመቀጠል ሞከረ፣ ነገር ግን የሞሮኒ ወታደሮችን ማሸነፍ አልቻለም። ከዚያም ዛራሔምና እና ሠራዊቱ በሰላም ለመኖር ቃል ገቡ፣ ሞሮኒም እንዲሄዱ ለቀቃቸው።

አልማ 44፥1–20

አትም