የሰማይ ሸንጎ ደግሞም ቅድመ ምድራዊ ህይወት; የሰማይ ጦርነት; የቤዛነት ዕቅድ ተመልከቱ በቅድመ ምድራዊ ህይወት ወደዚህች ምድር ለሚመጡት ለመንፈስ ልጆቹ አብ አላማውን ያቀረበበት ጊዜ። የእግዚአብሔርም ልጆች ሁሉ እልል አሉ, ኢዮብ ፴፰፥፬–፯. ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደርጋለሁ, ኢሳ. ፲፬፥፲፪–፲፫. በሰማይ ሰልፍ ሆነ, ራዕ. ፲፪፥፯–፲፩. ከመወላዳቸው በፊት፣ የመጀመሪያውን ትምህርት በመንፈሶች አለም ተቀበሉ, ት. እና ቃ. ፻፴፰፥፶፮. ሰይጣን በቅድመ ምድራዊ ህይወት አመጸ, ሙሴ ፬፥፩–፬. አለም ከመፈጠሯ በፊት እውቀተኛዎችም ተደራጅተው ነበር, አብር. ፫፥፳፪. አምላኮች ተመካከሩ, አብር. ፬፥፳፮. አምላኮች የተማከሩባቸውን ስራዎች ጨረሱ, አብር. ፭፥፪.